
አዳማ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)የ፦ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ከተማ አስተዳደሩ ገለፀ።
ስማርት አዳማ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በአገልግሎትና የአሰራር ማሻሻያ ጭምር በጥናት ላይ የተደገፉ ተግባራት ፕሮጀክት ያቀፈ ነው።
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ በሪሶ ዶሪ ለኢዜአ እንዳሉት በከተማዋ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል የስማርት አዳማ ፕሮጀክት እየተተገበሩ ነው።
ለፕሮጀክቱ ትግበራ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኢትዮ ቴሌኮምና አርተፊሻል እንቴለጀንስ ከፍተኛ ድጋፍና እገዛ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፕሮጄክቱ የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
በፕሮጀክቱ በከተማዋ የሁሉም መስሪያ ቤቶች ሰነዶችን ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ መሆኑን ገልጸው፤ የመሰረተ ልማት፣ የትፊክ ፍሰት፣ የትራንስፖርት አገልግሎትና የጸጥታ ተቋማትን ለአብነት አንስተዋል።
ከ81 ሺህ በላይ የመሬት አሰተዳደርና አጠቃቀም ፋይሎች ወደ ዲጂታል በመቀየር ሌብነትና ብልሹ አሰራርን ጨምሮ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
የኢትዮ-ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ለስማርት አዳማ ፕሮጀክት አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማትና የኮደርስ ስልጠናም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026