የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ፕሮጀክቱ የከተማዋን አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ እያደረገ ነው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)የ፦ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ከተማ አስተዳደሩ ገለፀ።

ስማርት አዳማ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በአገልግሎትና የአሰራር ማሻሻያ ጭምር በጥናት ላይ የተደገፉ ተግባራት ፕሮጀክት ያቀፈ ነው።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ በሪሶ ዶሪ ለኢዜአ እንዳሉት በከተማዋ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል የስማርት አዳማ ፕሮጀክት እየተተገበሩ ነው።

ለፕሮጀክቱ ትግበራ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኢትዮ ቴሌኮምና አርተፊሻል እንቴለጀንስ ከፍተኛ ድጋፍና እገዛ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፕሮጄክቱ የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በፕሮጀክቱ በከተማዋ የሁሉም መስሪያ ቤቶች ሰነዶችን ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ መሆኑን ገልጸው፤ የመሰረተ ልማት፣ የትፊክ ፍሰት፣ የትራንስፖርት አገልግሎትና የጸጥታ ተቋማትን ለአብነት አንስተዋል።

ከ81 ሺህ በላይ የመሬት አሰተዳደርና አጠቃቀም ፋይሎች ወደ ዲጂታል በመቀየር ሌብነትና ብልሹ አሰራርን ጨምሮ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።

የኢትዮ-ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ለስማርት አዳማ ፕሮጀክት አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማትና የኮደርስ ስልጠናም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026