
አዳማ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)የ፦ የስማርት አዳማ ፕሮጀክት የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ከተማ አስተዳደሩ ገለፀ።
ስማርት አዳማ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በአገልግሎትና የአሰራር ማሻሻያ ጭምር በጥናት ላይ የተደገፉ ተግባራት ፕሮጀክት ያቀፈ ነው።
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ በሪሶ ዶሪ ለኢዜአ እንዳሉት በከተማዋ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል የስማርት አዳማ ፕሮጀክት እየተተገበሩ ነው።
ለፕሮጀክቱ ትግበራ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኢትዮ ቴሌኮምና አርተፊሻል እንቴለጀንስ ከፍተኛ ድጋፍና እገዛ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፕሮጄክቱ የከተማዋ አገልግሎት አሰጣጥ ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
በፕሮጀክቱ በከተማዋ የሁሉም መስሪያ ቤቶች ሰነዶችን ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ መሆኑን ገልጸው፤ የመሰረተ ልማት፣ የትፊክ ፍሰት፣ የትራንስፖርት አገልግሎትና የጸጥታ ተቋማትን ለአብነት አንስተዋል።
ከ81 ሺህ በላይ የመሬት አሰተዳደርና አጠቃቀም ፋይሎች ወደ ዲጂታል በመቀየር ሌብነትና ብልሹ አሰራርን ጨምሮ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
የኢትዮ-ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ ለስማርት አዳማ ፕሮጀክት አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማትና የኮደርስ ስልጠናም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026