ቦንጋ ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱ ተገለጸ።
እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ መንግስት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀምና የፓርቲ ስራዎች የግምገማ መድረክ የኢንቨስትመንት አፈጻጸምም ቀርቧል።
የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን በቀለ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳሉት በክልሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 54 ባለሀብቶች ፍቃድ መሠጠቱንም ገልፀዋል።
ፈቃድ የተሰጠውም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም 7 ሺህ 635 ሄክታር የኢንቨስትመንት መሬት የመለየት ስራ መሠራቱንም ተናግረዋል።
ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያም ባለሀብቶችን በማስተባበር 55 ኪሎ ሜትር መዳረሻ መንገድ ግንባታ ማካሄድ እንደተቻለም ጠቁመዋል።
በነዚህ ወራት በክልሉ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች 10 ሺህ 435 ሄክታር መሬት ማስተላለፍ መቻሉንም ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ 70 ድርጅቶች ላይ የመሬት ኦዲት በማድረግ ወደ ስራ ያልገባ 10 ሺህ 295 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ገቢ መደረጉንም አንስተዋል።
በተመሳሳይ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ25 ሺህ ቶን በላይ የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 24 ነጥብ 9 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በተጨማሪም 21 ሺህ 877 ቶን የተለያየ ቅመማ ቅመም ምርት ለገበያ መቅረቡንም አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025