
ቦንጋ ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱ ተገለጸ።
እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ መንግስት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀምና የፓርቲ ስራዎች የግምገማ መድረክ የኢንቨስትመንት አፈጻጸምም ቀርቧል።
የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን በቀለ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳሉት በክልሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 54 ባለሀብቶች ፍቃድ መሠጠቱንም ገልፀዋል።
ፈቃድ የተሰጠውም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም 7 ሺህ 635 ሄክታር የኢንቨስትመንት መሬት የመለየት ስራ መሠራቱንም ተናግረዋል።
ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያም ባለሀብቶችን በማስተባበር 55 ኪሎ ሜትር መዳረሻ መንገድ ግንባታ ማካሄድ እንደተቻለም ጠቁመዋል።
በነዚህ ወራት በክልሉ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች 10 ሺህ 435 ሄክታር መሬት ማስተላለፍ መቻሉንም ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ 70 ድርጅቶች ላይ የመሬት ኦዲት በማድረግ ወደ ስራ ያልገባ 10 ሺህ 295 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ገቢ መደረጉንም አንስተዋል።
በተመሳሳይ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ25 ሺህ ቶን በላይ የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 24 ነጥብ 9 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በተጨማሪም 21 ሺህ 877 ቶን የተለያየ ቅመማ ቅመም ምርት ለገበያ መቅረቡንም አስረድተዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026