
ቦንጋ ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱ ተገለጸ።
እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ መንግስት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀምና የፓርቲ ስራዎች የግምገማ መድረክ የኢንቨስትመንት አፈጻጸምም ቀርቧል።
የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን በቀለ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳሉት በክልሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 54 ባለሀብቶች ፍቃድ መሠጠቱንም ገልፀዋል።
ፈቃድ የተሰጠውም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም 7 ሺህ 635 ሄክታር የኢንቨስትመንት መሬት የመለየት ስራ መሠራቱንም ተናግረዋል።
ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያም ባለሀብቶችን በማስተባበር 55 ኪሎ ሜትር መዳረሻ መንገድ ግንባታ ማካሄድ እንደተቻለም ጠቁመዋል።
በነዚህ ወራት በክልሉ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች 10 ሺህ 435 ሄክታር መሬት ማስተላለፍ መቻሉንም ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ 70 ድርጅቶች ላይ የመሬት ኦዲት በማድረግ ወደ ስራ ያልገባ 10 ሺህ 295 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ገቢ መደረጉንም አንስተዋል።
በተመሳሳይ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ25 ሺህ ቶን በላይ የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 24 ነጥብ 9 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በተጨማሪም 21 ሺህ 877 ቶን የተለያየ ቅመማ ቅመም ምርት ለገበያ መቅረቡንም አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026