
ቦንጋ ፤ጥር 28/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መሰጠቱ ተገለጸ።
እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ መንግስት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀምና የፓርቲ ስራዎች የግምገማ መድረክ የኢንቨስትመንት አፈጻጸምም ቀርቧል።
የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን በቀለ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳሉት በክልሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 54 ባለሀብቶች ፍቃድ መሠጠቱንም ገልፀዋል።
ፈቃድ የተሰጠውም በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም 7 ሺህ 635 ሄክታር የኢንቨስትመንት መሬት የመለየት ስራ መሠራቱንም ተናግረዋል።
ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አኳያም ባለሀብቶችን በማስተባበር 55 ኪሎ ሜትር መዳረሻ መንገድ ግንባታ ማካሄድ እንደተቻለም ጠቁመዋል።
በነዚህ ወራት በክልሉ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች 10 ሺህ 435 ሄክታር መሬት ማስተላለፍ መቻሉንም ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ 70 ድርጅቶች ላይ የመሬት ኦዲት በማድረግ ወደ ስራ ያልገባ 10 ሺህ 295 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ገቢ መደረጉንም አንስተዋል።
በተመሳሳይ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ25 ሺህ ቶን በላይ የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 24 ነጥብ 9 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በተጨማሪም 21 ሺህ 877 ቶን የተለያየ ቅመማ ቅመም ምርት ለገበያ መቅረቡንም አስረድተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026