
ጭሮ/ጊምቢ/መቱ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ሶስት ዞኖች ባለፉት ስድስት ወራት ከ200 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የስራ መስኮች እንዲሰማሩ መደረጉን የየዞኖቹ ስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ጽህፈት ቤቶች ገልጸዋል፡፡
የስራ እድሉ የተፈጠረው በክልሉ ምዕራብ ሐረርጌ፣ ምዕራብ ወለጋ እና ኢሉአባቦር ዞኖች ሲሆን ወጣቶቹም በስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የክህሎት ስልጠና የብድርና የማምረቻ ቦታ መሰጠቱም ተገልጿል።
የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራ እና ክህሎት ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ አይናለም ጌታቸው እንዳሉት ባለፉት ስድስት ወራት ከ46 ሺህ 900 በላይ ወጣቶች በማህበራት ተደራጅተው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡
ለወጣቶቹ ከ76 ሚሊዮን ብር በላይ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ከ1 ሺህ ሄክታር በላይ የመስሪያ ቦታ ማቅረብ እንዲሁም የሙያ ስልጠና መሰጠቱን አብራርተዋል፡፡
የምዕራብ ወለጋ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራ እና ክህሎት ጽህፈት ቤት የከተማ ስራ ዕድል ፈጠራ ቡድን መሪ አቶ ሀምቢሳ ተርፋ፤ በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት ከ99 ሺህ በላይ ወጣቶችን በገጠርና በከተሞች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ለወጣቶቹ ከ2 ሺህ ሄክታር በላይ የመስሪያ ቦታ መሬትና ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ በኢሉአባቦር ዞን ባለፉት ስድት ወራት ከ58 ሺህ 800 በላይ ወጣቶች በተለያዩ የስራ መስኮች የስራ ዕድል መፈጠሩን የዞኑ የስራ ዕድል ፈጠራና ሙያ ጽህፈት ቤት የዕቅድ ግምገማና ክትትል ስራ ሂደት መሪ አቶ ወንድሙ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
የስራ እድል ከተፈጠረላችው ወጣቶች መካከል በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በጭሮ ከተማ በማህበር ተደራጅተው በዶሮ እርባታ የተሰማሩት ወጣት ሚሊኪ ያኪ እና ጓደኞቹ በተመቻቸላቸው የ500 ሺህ ብር ብድር በጀመሩት ስራ ውጤታማ በመሆኑ ብድሩን ከመመለስ አልፎ ከ200 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግሯል፡፡
የዚሁ ከተማ ወጣት ደምሴ ከተማ ከአምስት ጓደኞቹ ጋር በመደራጀት 100 ሺህ ብር ተበድረው በጀመሩት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ጥገና እና ንግድ ስራ ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በምዕራብ ወለጋ ዞን፤ ወጣት ዳንኤል ዱጋሳ ከጓደኞቹ ጋር በማህበር የጀመሩት የሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ ውጤታማ እያደረጋቸው መምጣቱን አስረድተዋል፡፡
ከስራ እድል ተጠቃሚዎች መካከል በኢሉአባቦር ዞን ሀሉ ወረዳ በሻይ ልማት መስክ የተሰማራው ወጣት ታረቀኝ አስፋው እንዳለው የሻይ ቅጠልን ለገበያ በማቅረብ ገቢውን ለማሳደግ እየሰራ ነው፡፡
የዞኑ መንግስት ብዝሀ ኢኮኖሚን ለማስፋት ለሻይ ልማት የተሰጠው ትኩረትና ምርቱ በገበያ ተፈላጊ መሆኑ ገቢውን እንዳሳደገለት ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026