የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ሀገር በቀል ዕውቀቶች ለሰላምና አብሮነት ያላቸውን አበርክቶ ለማጎልበት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ ጥር 29/ 2017(ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል ዕውቀቶች ለሀገራዊ ሰላም፣ አብሮነት እና ለሥራ ፈጠራ ያላቸውን አበርክቶ ለማጎልበት ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

"ሀገር በቀል እውቀት ለሀገራዊ ልማት" በሚል መሪ ቃል 7ኛው ሀገራዊ የሀገር በቀል ዕውቀት ዐውደ ጥናት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።

በዐውደ ጥናቱም ሀገር በቀል ዕውቀትን መሰረት ያደረጉ 10 የምርምር ውጤቶች በምሁራን ቀርበው ውይይት ተደርጓባቸዋል።

በሚኒስቴሩ የባህል እሴቶችና ሀገር በቀል እውቀቶች ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ እስከዳር ግሩም ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የበዙ ባህላዊና ሀገር በቀል እውቀቶች ባለቤት ናት።

ለዚህም የዕደ ጥበብ ውጤት፣ የግጭት አፈታት ሥርዓት፣ የዘመን አቆጣጠር እንዲሁም የባህል ህክምና፣ የእርከንና የግብርና ልማት ተጠቃሽ ሀገር በቀል እውቀቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የለውጡ መንግስት ለባህል እሳቤዎች ትኩረት መስጠቱ ሀገር በቀል እውቀቶች በምርምር እንዲዳብሩ አቅም መፍጠሩን ጠቅሰዋል።

ይህን ለማጠናከር በተለይ ሀገር በቀል እውቀት ለሀገራዊ ሰላም፣ አንድነትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን አበርክቶ ለማጠናከር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል።

የጌዴኦ የዘመን መለወጫ የዳራሮ በዓልን ምክንያት በማድረግ አውደ ጥናቱ በየዓመቱ እንደሚዘጋጅ ያነሱት ደግሞ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኤልያስ ዓለሙ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል እውቀቶችን ለማበልጸግ ትምህርትና ስልጠና ከመስጠት ባለፈ የተለያዩ ጥናትና ምርምሮችን በጋራና በተናጠል እያከናወነ ይግኛል ብለዋል።

በዚህም ሀገር በቀል እውቀቶች ከትምህርት አልፎ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ውስጥ የጎላ ሚና እንዲኖራቸው ዩኒቨርሲቲው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለሀገር በቀል እውቀቶች የተሰጠው ትኩረት ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ የሚሰጥ ማህበረሰብ ለመፍጠር የራሱ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ በበኩላቸው በዩኔስኮ የተመዘገበው የጌዴኦ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር የሀገር በቀል እውቀት ትሩፋት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሀገር በቀል እውቀት ለማህበረሰቡ ቅርብና ለመረዳት ቀላይ በመሆኑ ተመራጭ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለትውልድ እንዲሸጋገር የመንከባከብና የመጠበቅ ሥራ ይሰራል ብለዋል።

ባህላዊ እውቀትን በአግባቡ ሰንዶ ለማቆየት በሚሰራው ሥራ አውድ ጥናቱ ሚናው የጎላ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአውደ ጥናቱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች የባህል ሽማግሌዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የተለያዩ የሥራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026