
ዲላ፤ ጥር 29/ 2017(ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል ዕውቀቶች ለሀገራዊ ሰላም፣ አብሮነት እና ለሥራ ፈጠራ ያላቸውን አበርክቶ ለማጎልበት ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
"ሀገር በቀል እውቀት ለሀገራዊ ልማት" በሚል መሪ ቃል 7ኛው ሀገራዊ የሀገር በቀል ዕውቀት ዐውደ ጥናት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።
በዐውደ ጥናቱም ሀገር በቀል ዕውቀትን መሰረት ያደረጉ 10 የምርምር ውጤቶች በምሁራን ቀርበው ውይይት ተደርጓባቸዋል።
በሚኒስቴሩ የባህል እሴቶችና ሀገር በቀል እውቀቶች ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ እስከዳር ግሩም ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የበዙ ባህላዊና ሀገር በቀል እውቀቶች ባለቤት ናት።
ለዚህም የዕደ ጥበብ ውጤት፣ የግጭት አፈታት ሥርዓት፣ የዘመን አቆጣጠር እንዲሁም የባህል ህክምና፣ የእርከንና የግብርና ልማት ተጠቃሽ ሀገር በቀል እውቀቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የለውጡ መንግስት ለባህል እሳቤዎች ትኩረት መስጠቱ ሀገር በቀል እውቀቶች በምርምር እንዲዳብሩ አቅም መፍጠሩን ጠቅሰዋል።
ይህን ለማጠናከር በተለይ ሀገር በቀል እውቀት ለሀገራዊ ሰላም፣ አንድነትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን አበርክቶ ለማጠናከር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል።
የጌዴኦ የዘመን መለወጫ የዳራሮ በዓልን ምክንያት በማድረግ አውደ ጥናቱ በየዓመቱ እንደሚዘጋጅ ያነሱት ደግሞ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኤልያስ ዓለሙ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል እውቀቶችን ለማበልጸግ ትምህርትና ስልጠና ከመስጠት ባለፈ የተለያዩ ጥናትና ምርምሮችን በጋራና በተናጠል እያከናወነ ይግኛል ብለዋል።
በዚህም ሀገር በቀል እውቀቶች ከትምህርት አልፎ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ውስጥ የጎላ ሚና እንዲኖራቸው ዩኒቨርሲቲው እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ለሀገር በቀል እውቀቶች የተሰጠው ትኩረት ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ የሚሰጥ ማህበረሰብ ለመፍጠር የራሱ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል።
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ በበኩላቸው በዩኔስኮ የተመዘገበው የጌዴኦ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር የሀገር በቀል እውቀት ትሩፋት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሀገር በቀል እውቀት ለማህበረሰቡ ቅርብና ለመረዳት ቀላይ በመሆኑ ተመራጭ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለትውልድ እንዲሸጋገር የመንከባከብና የመጠበቅ ሥራ ይሰራል ብለዋል።

ባህላዊ እውቀትን በአግባቡ ሰንዶ ለማቆየት በሚሰራው ሥራ አውድ ጥናቱ ሚናው የጎላ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በአውደ ጥናቱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች የባህል ሽማግሌዎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የተለያዩ የሥራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026