
ቦንጋ፤ጥር 29/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገቡ የልማት ውጤቶችን በማስቀጠል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
በቦንጋ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክልሉ መንግስት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተጠናቋል።

በክልሉ በተለያዩ መስኮች የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማጠናከር ለጥራት፣ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብና ልማትን ለማፋጠን ትኩረት እንደሚሰጥም ተናግረዋል።
ገበያን ለማረጋጋት ከሚከናወኑ ተግባራት በተጨማሪ በመሠረተ ልማትና በማህበራዊ ዘርፎች ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት በተለያዩ የልማት መስኮች የተመዘገቡ ውጤቶችን በማጠናከርና ጉድለቶችን በማረም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራም ገልጸዋል።
የልማት ሥራዎችን የሚያደናቅፉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ለማስቀጠል የህግ ተጠያቂነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የገለጹት።
ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የችግኝ ተከላ ዝግጅት፣ የበልግ አዝመራ ሥራ፣የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከሚሰራው ሥራ በተጨማሪ ነዳጅን ጨምሮ በተለያዩ ምርቶች ላይ የሚስተዋለውን ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ለመከላከል ይሰራል ብለዋል።
የሌማት ትሩፋትና የመስኖ ልማትን ጨምሮ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን የገበያ ማረጋጋቱ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
በየመስኩ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል አመራሩ በየአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ ወደልማት ለመቀየር ትኩረት ማድረግ እንዳለበት የገለጹት ደግሞ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።
ለዚህም ከተለመደው አሰራር አለፍ ብሎ ህብረተሰቡን በቅርበት በመደገፍ ተግቶ መስራት እንዳለበት ገልጸዋል።
በተለይ በግብርና ዘርፍ የአርሶ አደሩን ሕይወት በተጨባጭ ለመቀየር በግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያለውን ተግዳሮት መፍታት ቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
በከተሞች ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ማረምና የተለያዩ የልማት ኦኒሺየቲቮችን ማስፋት እንደሚገባም አንስተዋል።
የግምገማ መድረኩ ለቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026