የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት ለመውጣት የተጀመረው ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት ለመውጣት የተጀመረው ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

የክልሉ የአስፈጻሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ተጠናቋል።

በግምገማው በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ እና የበለጠ መስራትን የሚጠይቁ ናቸው ብለዋል።


በተለይ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደረጉ መሆናቸውን አንስተው የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን ማስፋፋት ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል።

የሌማት ትሩፋት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የገቢ ምንጭ እና የኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን አንስተው የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት ለመውጣት የተጀመረው ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የልማት ስራዎችን በማስፋት ምርታማነትን ለማሳደግ በሁሉም አካባቢዎች የተጀመሩ ስራዎች በልዩ ትኩረት የሚከናወኑ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በክልሉ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ፣ የቴሌኮም መሠረተ ልማት ግንባታዎችን ለማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን ለማጠናከር ከፌዴራል መንግስት ጋር በቅርበት እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የትምህርት፣ የጤና እና የውሃ ፕሮጀክቶች የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ የጥገና እና የመልሶ ግንባታ ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የመምህራንን አቅም ማሳደግ እንዲሁም የተማሪዎች ምገባ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።

በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም እየተሻሻለ ቢሆንም አሁንም ገቢ በሚያስገኙ ስራዎች ላይ ክትትል እና ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዘንደሮ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 2 ቢሊዮን 250 ሚሊዮን ገቢ መሰብሰቡን ጠቅሰው ይህም ከእቅዱ 98 በመቶ የተሳካበት መሆኑን ገልጸዋል።

በአምስት ሚሊየን የኮደርስ ስልጠና በክልሉ እስከ አሁን አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረው ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት ሌሎችም እንዲሰለጥኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026