የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት ለመውጣት የተጀመረው ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት ለመውጣት የተጀመረው ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

የክልሉ የአስፈጻሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ተጠናቋል።

በግምገማው በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ እና የበለጠ መስራትን የሚጠይቁ ናቸው ብለዋል።


በተለይ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደረጉ መሆናቸውን አንስተው የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን ማስፋፋት ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል።

የሌማት ትሩፋት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የገቢ ምንጭ እና የኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን አንስተው የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ከተረጅነት ለመውጣት የተጀመረው ሁሉን አቀፍ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የልማት ስራዎችን በማስፋት ምርታማነትን ለማሳደግ በሁሉም አካባቢዎች የተጀመሩ ስራዎች በልዩ ትኩረት የሚከናወኑ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በክልሉ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ፣ የቴሌኮም መሠረተ ልማት ግንባታዎችን ለማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን ለማጠናከር ከፌዴራል መንግስት ጋር በቅርበት እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የትምህርት፣ የጤና እና የውሃ ፕሮጀክቶች የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ የጥገና እና የመልሶ ግንባታ ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የመምህራንን አቅም ማሳደግ እንዲሁም የተማሪዎች ምገባ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።

በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም እየተሻሻለ ቢሆንም አሁንም ገቢ በሚያስገኙ ስራዎች ላይ ክትትል እና ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዘንደሮ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 2 ቢሊዮን 250 ሚሊዮን ገቢ መሰብሰቡን ጠቅሰው ይህም ከእቅዱ 98 በመቶ የተሳካበት መሆኑን ገልጸዋል።

በአምስት ሚሊየን የኮደርስ ስልጠና በክልሉ እስከ አሁን አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረው ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት ሌሎችም እንዲሰለጥኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026