አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት ባለፋት ስድስት ወራት 169 የDNA ምርመራ ማከናወኑን ገልጿል።
ውጤቱ የተመዘገበው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ የDNA ምርመራ ላቦራቶሪ በማደራጀትና በዘርፉ ተገቢው ሙያዊ ዕውቀት ያላቸው ባለሙያዎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር አሰልጥኖ ወደ ሥራ በማሰማራቱ መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።
ከለውጡ በፊት በሀገር ውስጥ የDNA ምርመራ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ባለመኖሩ ናሙና ወደ ውጭ ሀገር እየተላከ በከፍተኛ ወጪ ሲመረመር እንደነበር አስታውሶ ይህን አሠራር በማስቀረት በሀገር ውስጥ የDNA የምርመራ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጿል፡፡
የDNA ምርመራ ለፍትህ ሥርዓት መረጋገጥ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሶ በተለይ የሰዎችን ማንነት ለመለየት፤ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ለማረጋገጥ፣ ከተወላጅነት ጋር ለሚነሱ ክርክሮችና ቤተሰባዊ ጉዳዮችን ለመመርመር የሚያስችል አቅም እንደተፈጠረም ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025