
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት ባለፋት ስድስት ወራት 169 የDNA ምርመራ ማከናወኑን ገልጿል።
ውጤቱ የተመዘገበው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ የDNA ምርመራ ላቦራቶሪ በማደራጀትና በዘርፉ ተገቢው ሙያዊ ዕውቀት ያላቸው ባለሙያዎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር አሰልጥኖ ወደ ሥራ በማሰማራቱ መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።

ከለውጡ በፊት በሀገር ውስጥ የDNA ምርመራ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ባለመኖሩ ናሙና ወደ ውጭ ሀገር እየተላከ በከፍተኛ ወጪ ሲመረመር እንደነበር አስታውሶ ይህን አሠራር በማስቀረት በሀገር ውስጥ የDNA የምርመራ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጿል፡፡
የDNA ምርመራ ለፍትህ ሥርዓት መረጋገጥ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሶ በተለይ የሰዎችን ማንነት ለመለየት፤ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ለማረጋገጥ፣ ከተወላጅነት ጋር ለሚነሱ ክርክሮችና ቤተሰባዊ ጉዳዮችን ለመመርመር የሚያስችል አቅም እንደተፈጠረም ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026