የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የፈጠራ ሀሳቦች ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዕውቀት መር የቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረት የሚጥሉ ናቸው</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦የፈጠራ ሀሳቦች ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዕውቀት መር የቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡

በሀገሪቱ የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት ፕሮግራም ይፋ ሆኗል።

የፈጠራ ውድድሩንየስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንተርፕርነር ሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት፣ እናት ባንክና በተባበሩት መንግስታት የሴቶች ጉዳይ በጋራ "ብሩህ እናት" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ ነው።


የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በዚህ ወቅት፤ በሀገሪቱ የሚስተዋለውን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጸው፤ ከአጋር አካላት ጋር በመተባባር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ዛሬ ይፋ የተደረገውፕሮግራም ፈጠራ ሃሳብን ከማበረታታት ባለፈ ሴቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች መፍትሔ ማመንጫ መንገድ ነው ብለዋል፡፡

በዚህምየፈጠራ ሀሳቦች ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዕውቀት መር የቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ከሚመዘገቡ ሴቶች መካከል 50 ሴቶች በፈጠራ ሀሳባቸው ተለይተው ከመጋቢት 8 እስከ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ስልጠና ገብተው በፈጠራ ሀሳቦቻቸው ዙሪያ የሚሰለጥኑበት፣ የሚበቁበትና 10 አሸናፊዎች የሚለዩበት ይሆናል ብለዋል፡፡

ችግር ፈቺና ተጨባጭ የሆኑ ፈጠራ ሀሳቦች ወደ ተቋማዊነት የማሸጋገር እና ለአሸናፊዎቹ የብድርና መስሪያ ቦታም እንደሚመቻች ገልጸዋል፡፡


የኢንተርፕርነር ሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦሩ ሸና በበኩላቸው ኢንተርፕነር ሽፕ እንደ ሀገር ባህል ሆኖ እንዲጎለብትና ግለሰቦችም የራሳቸውን አቅም በመጠቀም ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራን በትኩረት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሀገሪቱ የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች የሚወዳደሩባቸው መስፈርትም በገበያ ተፈላጊነት እና ባለው አቅም በቀላሉ መሰራታቸው ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡

የእናት ባንክ ኦፕሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ትዕግስት አባተ በበኩላቸው፤ የሴቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።


የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት የሴቶችን ክህሎት የሚያዳብርና ችግራቸውን የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡

ባንኩ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች በደረጃቸው ከ100 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር እንደሚሸልም ገልጸዋል፡፡

የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት ፕሮግራም ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 24 ቀን 2017 በሚከተለው ሊንክ መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

https://docs.google.com/forms/d/1vhHo lorWka27YYhisK1BIrnEQ27NOMomKeI7FCUB1Q/edit?edit_requested=true

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026