የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የፈጠራ ሀሳቦች ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዕውቀት መር የቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረት የሚጥሉ ናቸው</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦የፈጠራ ሀሳቦች ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዕውቀት መር የቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ፡፡

በሀገሪቱ የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት ፕሮግራም ይፋ ሆኗል።

የፈጠራ ውድድሩንየስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢንተርፕርነር ሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት፣ እናት ባንክና በተባበሩት መንግስታት የሴቶች ጉዳይ በጋራ "ብሩህ እናት" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ ነው።


የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በዚህ ወቅት፤ በሀገሪቱ የሚስተዋለውን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጸው፤ ከአጋር አካላት ጋር በመተባባር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ዛሬ ይፋ የተደረገውፕሮግራም ፈጠራ ሃሳብን ከማበረታታት ባለፈ ሴቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች መፍትሔ ማመንጫ መንገድ ነው ብለዋል፡፡

በዚህምየፈጠራ ሀሳቦች ኢትዮጵያ ለጀመረችው ዕውቀት መር የቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ከሚመዘገቡ ሴቶች መካከል 50 ሴቶች በፈጠራ ሀሳባቸው ተለይተው ከመጋቢት 8 እስከ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ስልጠና ገብተው በፈጠራ ሀሳቦቻቸው ዙሪያ የሚሰለጥኑበት፣ የሚበቁበትና 10 አሸናፊዎች የሚለዩበት ይሆናል ብለዋል፡፡

ችግር ፈቺና ተጨባጭ የሆኑ ፈጠራ ሀሳቦች ወደ ተቋማዊነት የማሸጋገር እና ለአሸናፊዎቹ የብድርና መስሪያ ቦታም እንደሚመቻች ገልጸዋል፡፡


የኢንተርፕርነር ሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦሩ ሸና በበኩላቸው ኢንተርፕነር ሽፕ እንደ ሀገር ባህል ሆኖ እንዲጎለብትና ግለሰቦችም የራሳቸውን አቅም በመጠቀም ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራን በትኩረት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሀገሪቱ የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች የሚወዳደሩባቸው መስፈርትም በገበያ ተፈላጊነት እና ባለው አቅም በቀላሉ መሰራታቸው ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡

የእናት ባንክ ኦፕሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ትዕግስት አባተ በበኩላቸው፤ የሴቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።


የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት የሴቶችን ክህሎት የሚያዳብርና ችግራቸውን የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡

ባንኩ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች በደረጃቸው ከ100 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር እንደሚሸልም ገልጸዋል፡፡

የቢዝነስ ፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት ፕሮግራም ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 24 ቀን 2017 በሚከተለው ሊንክ መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

https://docs.google.com/forms/d/1vhHo lorWka27YYhisK1BIrnEQ27NOMomKeI7FCUB1Q/edit?edit_requested=true

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026