የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ አካታች የኢኮኖሚና ማህበራዊ አገልግሎት ስርዓትን በማፋጠን ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ አካታች የኢኮኖሚና ማህበራዊ አገልግሎት ስርዓትን በማፋጠን ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ።

ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ የግለሰቦችን ማንነት ለማረጋገጥና አገልግሎትን ለማሻሻል ትልቅ ሚና እንዳለውም ገልጿል።

በኢትዮጵያ ነዋሪዎች ማንኛውንም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ አገልግሎቶችን ማግኘት የሚችሉበት የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል፡፡

አዋጁ ነዋሪዎች የመታወቅ መብታቸው እንዲረጋገጥ፣ ሌሎች መብቶቻቸውን የመጠቀም እድላቸውን ለማስፋት፤ በአገልግሎት ሰጭና ተቀባይ መካከል በሚኖር ግንኙነት እምነት እንዲዳብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና የተሳለጠ አሰራር መዘርጋትን ያለመ ነው፡፡


የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ ራሄል ይትባረክ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮ አንጻር ሲታይ ኢትዮጵያ በፍጥነት የገባችበት ነው፡፡

ከተቋማት ጋር ያለው ትስስር እና የማህበረሰቡ ግንዛቤ በየጊዜው እየዳበረ በመምጣቱ የተመዝጋቢዎች ቁጥር በፍጥነት እያደገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ በአዋጅ ተቋቁሞ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ እስካሁን 12 ሚሊዮን ያህል ነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ለማግኘት ተመዝግበዋል ብለዋል።


የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቤኔዘር ፈለቀ በበኩላቸው፣ ማንኛውም ለዲጂታል መታወቂያ የባዮሜትሪክ እና የዲሞግራፊ መረጃ በመስጠት የተመዘገበ ሰው መታወቂያውን የማግኘት መብት እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ማንኛውም ነዋሪ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የሚያከናውነው የተሳለጠ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚጠቅመው ተረድቶ በራሱ ፍላጎትና ፈቃድ ብቻ እንደሆነ በአዋጁ ተገልጿል ብለዋል፡፡

ነገር ግን ተቋማት ውስጣዊ አሰራራቸውን ለማዘመን ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያን አስገዳጅ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

ለአብነትም ብሔራዊ ባንክ ከታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ(የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብን እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።

ተቋማት የፋይዳ መታወቂያ መያዝን አስገዳጅ ሲያደርጉ ተገልጋዮች መጉላላት እንዳይገጥማቸው ብሔራዊ የመታወቂያ ፕሮግራም የተቀላጠፈ ምዝገባ የማድረግ ግዴታውን ይወጣል ብለዋል፡፡

ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ አካታች የኢኮኖሚና ማህበራዊ አገልግሎት ስርዓትን በማፋጠን ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም የፋይዳ ተመዝጋቢዎች የዲጂታል መታወቂያውን በዲጂታል ቅጂ፣ በወረቀት ወይም በካርድ በማሳተም መያዝ ይችላሉ ብለዋል፡፡

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ ራሄል ይትባረክ፥ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ያለ ክፍያ እንደሚፈጸም ጠቅሰዋል።

ነገር ግን ፋይዳን በካርድ አትሞ ለመስጠት ተቋማት እንደ ግለሰቦች ፍላጎት የተለያየ መጠን ያለው ክፍያ እንደሚጠይቁ ገልጸዋል።

አንድ ሰው ለዲጂታል መታወቂያ የተጠየቀውን መረጃ አሟልቶ ከተመዘገበ በኋላ ከ30 ደቂቃ እስከ 7 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ የፋይዳ ቁጥሩን የማግኘት መብት እንዳለው ተናግረዋል፡፡

ግለሰቡ ሁለት ቦታ ላይ ከተመዘገበ መዘግየት ሊያጋጥም እንደሚችል ገልጸው፤ አሁን ላይ ተቋሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተናበበ አሰራርን የሚከተል በመሆኑ ችግሩ መፈታቱን ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ አገልግሎቱን በሁሉም ክልሎች በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የምዝገባ ቁሳቁሶች በስርጭት ላይ መሆናቸውንም አመላክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026