የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ሲሉ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

የ‘ክህሎት ኢትዮጵያ’ ተሳታፊ ቴክኖሎጂስቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን እና የሰሯቸውን ፕሮቶታይፖች አቅርበዋል፡፡


ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ብለዋል፡፡

ለፕሮግራሙ ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ኢንስቲትዩቱ እና የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት የቅርብ ክትትል ያለው መሆኑን አንስተዋል።

የፕሮግራሙ ስኬት የጽናት ማሳያ ነው፤ ይህም የአመራር፣ የሙያተኛ፣ የተሳታፊዎችም ጽናት የታየበት ነው ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡


የተጀመሩ የፈጠራ ስራዎች ከፕሮቶታይፕ አልፈው ምርት እስከሚጀመሩ ድረስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፉንና ክትትሉን እንደማያቆም መናገራቸውን ከኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው ሁለተኛው ዙር ፕሮግራም ከመጀመሪያው ይልቅ ብዙ ትምህርት የተወሰደበት እና ብዙ መሻሻሎች የታየበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ከዚህም መካከል በጥብቅ የመረጣ ሂደት ውስጥ ማለፉን፣ የኢንደስትሪ ልምምድ በስፋት መካሄዱን፣ የተግባቦት ክህሎታቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ማግኘታቸውን አንስተዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ይህ ፕሮግራም ሀገር በቀል በሆነ እሳቤ በሀገር ልጅ ቴክኖሎጂስቶች ችግርን የመፍታት ሐሳብ የወለደው ፕሮግራም መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ባለቤቶች የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ትኩረት በሆኑት ግብርና፣ ጤና፣ ቱሪዝም፣ ኮንስትራክሸን፣ አይሲቲ፣ ሀይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉብንን ችግሮች የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎቻቸውን አቅርበዋል ነው ያሉት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025