
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ሲሉ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
የ‘ክህሎት ኢትዮጵያ’ ተሳታፊ ቴክኖሎጂስቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን እና የሰሯቸውን ፕሮቶታይፖች አቅርበዋል፡፡

ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ብለዋል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ኢንስቲትዩቱ እና የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት የቅርብ ክትትል ያለው መሆኑን አንስተዋል።
የፕሮግራሙ ስኬት የጽናት ማሳያ ነው፤ ይህም የአመራር፣ የሙያተኛ፣ የተሳታፊዎችም ጽናት የታየበት ነው ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡

የተጀመሩ የፈጠራ ስራዎች ከፕሮቶታይፕ አልፈው ምርት እስከሚጀመሩ ድረስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፉንና ክትትሉን እንደማያቆም መናገራቸውን ከኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው ሁለተኛው ዙር ፕሮግራም ከመጀመሪያው ይልቅ ብዙ ትምህርት የተወሰደበት እና ብዙ መሻሻሎች የታየበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ከዚህም መካከል በጥብቅ የመረጣ ሂደት ውስጥ ማለፉን፣ የኢንደስትሪ ልምምድ በስፋት መካሄዱን፣ የተግባቦት ክህሎታቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ማግኘታቸውን አንስተዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ይህ ፕሮግራም ሀገር በቀል በሆነ እሳቤ በሀገር ልጅ ቴክኖሎጂስቶች ችግርን የመፍታት ሐሳብ የወለደው ፕሮግራም መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡
የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ባለቤቶች የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ትኩረት በሆኑት ግብርና፣ ጤና፣ ቱሪዝም፣ ኮንስትራክሸን፣ አይሲቲ፣ ሀይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉብንን ችግሮች የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎቻቸውን አቅርበዋል ነው ያሉት፡፡
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026