የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ሲሉ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

የ‘ክህሎት ኢትዮጵያ’ ተሳታፊ ቴክኖሎጂስቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን እና የሰሯቸውን ፕሮቶታይፖች አቅርበዋል፡፡


ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ብለዋል፡፡

ለፕሮግራሙ ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ኢንስቲትዩቱ እና የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት የቅርብ ክትትል ያለው መሆኑን አንስተዋል።

የፕሮግራሙ ስኬት የጽናት ማሳያ ነው፤ ይህም የአመራር፣ የሙያተኛ፣ የተሳታፊዎችም ጽናት የታየበት ነው ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡


የተጀመሩ የፈጠራ ስራዎች ከፕሮቶታይፕ አልፈው ምርት እስከሚጀመሩ ድረስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፉንና ክትትሉን እንደማያቆም መናገራቸውን ከኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው ሁለተኛው ዙር ፕሮግራም ከመጀመሪያው ይልቅ ብዙ ትምህርት የተወሰደበት እና ብዙ መሻሻሎች የታየበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ከዚህም መካከል በጥብቅ የመረጣ ሂደት ውስጥ ማለፉን፣ የኢንደስትሪ ልምምድ በስፋት መካሄዱን፣ የተግባቦት ክህሎታቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ማግኘታቸውን አንስተዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ይህ ፕሮግራም ሀገር በቀል በሆነ እሳቤ በሀገር ልጅ ቴክኖሎጂስቶች ችግርን የመፍታት ሐሳብ የወለደው ፕሮግራም መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ባለቤቶች የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ትኩረት በሆኑት ግብርና፣ ጤና፣ ቱሪዝም፣ ኮንስትራክሸን፣ አይሲቲ፣ ሀይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉብንን ችግሮች የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎቻቸውን አቅርበዋል ነው ያሉት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026