
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ሲሉ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
የ‘ክህሎት ኢትዮጵያ’ ተሳታፊ ቴክኖሎጂስቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን እና የሰሯቸውን ፕሮቶታይፖች አቅርበዋል፡፡

ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም ሀገር በልጆቿ መልሳ የምትሰራበትን እድል የሚፈጥር ሂደት ነው ብለዋል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ኢንስቲትዩቱ እና የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት የቅርብ ክትትል ያለው መሆኑን አንስተዋል።
የፕሮግራሙ ስኬት የጽናት ማሳያ ነው፤ ይህም የአመራር፣ የሙያተኛ፣ የተሳታፊዎችም ጽናት የታየበት ነው ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡

የተጀመሩ የፈጠራ ስራዎች ከፕሮቶታይፕ አልፈው ምርት እስከሚጀመሩ ድረስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፉንና ክትትሉን እንደማያቆም መናገራቸውን ከኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው ሁለተኛው ዙር ፕሮግራም ከመጀመሪያው ይልቅ ብዙ ትምህርት የተወሰደበት እና ብዙ መሻሻሎች የታየበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ከዚህም መካከል በጥብቅ የመረጣ ሂደት ውስጥ ማለፉን፣ የኢንደስትሪ ልምምድ በስፋት መካሄዱን፣ የተግባቦት ክህሎታቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ማግኘታቸውን አንስተዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ይህ ፕሮግራም ሀገር በቀል በሆነ እሳቤ በሀገር ልጅ ቴክኖሎጂስቶች ችግርን የመፍታት ሐሳብ የወለደው ፕሮግራም መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡
የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ባለቤቶች የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ትኩረት በሆኑት ግብርና፣ ጤና፣ ቱሪዝም፣ ኮንስትራክሸን፣ አይሲቲ፣ ሀይልና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉብንን ችግሮች የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎቻቸውን አቅርበዋል ነው ያሉት፡፡
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026