የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የመንገድ ፕሮጀክቶች በወቅቱ እንዲጠናቀቁ የሚደረገው ክትትል ይጠናከራል- ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ የሚደረገው ክትትልና ዕገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።

ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች የክልል አመራሮች በፌደራልና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ያሉ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ተመልክተዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በክልሉ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው።

ፕሮጀክቶቹ በወቅቱ እንዲጠናቀቁ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው አሁናዊ አፈጻጸማቸው በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሆነ አመልክተዋል።

የፌደራል መንግስት ባሳየው ቁርጠኝነትም የሀዌላ ቱላ-ውጅግራ-ያዬ-ወራንቻ የ85 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ግንባታ መጀመሩን ተናግረዋል ።

በአዲስ መልክ የተጀመረው የመንገዱ ግንባታ አፈጻጸም የተሻለ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸው በቀጣይም ተገቢው ክትትልና እገዛ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


የጉብኝቱ ዓላማም የመንገድ መሰረተ ልማቶች ግንባታ በተያዘላቸው ጊዜ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲጀምሩ በማድረግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን አስታውቀዋል።

የክልሉ የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በበኩላቸው በክልሉ በርካታ የአዳዲስ መንገዶችና ድልድዮች ግንባታና ጥገና ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም 149 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 19 የመንገድ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የአፈር ስራ የሚከናወንባቸውን 10 የመንገድ ፕሮጀክቶችን በዘንድሮ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


የአስራ አንድ ድልድዮች ግንባታ አፈጻጻምም 70 ከመቶ መድረሱን ጠቅሰው በገጠር ተደራሽ መንገድ (URAP) ፕሮግራምም ከ136 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጻም የተሻለ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው "ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውም ጉልህ ነው" ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025