
ሀዋሳ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ የሚደረገው ክትትልና ዕገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።
ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች የክልል አመራሮች በፌደራልና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ያሉ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ተመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በክልሉ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው።
ፕሮጀክቶቹ በወቅቱ እንዲጠናቀቁ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው አሁናዊ አፈጻጸማቸው በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሆነ አመልክተዋል።
የፌደራል መንግስት ባሳየው ቁርጠኝነትም የሀዌላ ቱላ-ውጅግራ-ያዬ-ወራንቻ የ85 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ግንባታ መጀመሩን ተናግረዋል ።
በአዲስ መልክ የተጀመረው የመንገዱ ግንባታ አፈጻጸም የተሻለ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸው በቀጣይም ተገቢው ክትትልና እገዛ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የጉብኝቱ ዓላማም የመንገድ መሰረተ ልማቶች ግንባታ በተያዘላቸው ጊዜ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲጀምሩ በማድረግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን አስታውቀዋል።
የክልሉ የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በበኩላቸው በክልሉ በርካታ የአዳዲስ መንገዶችና ድልድዮች ግንባታና ጥገና ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም 149 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 19 የመንገድ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የአፈር ስራ የሚከናወንባቸውን 10 የመንገድ ፕሮጀክቶችን በዘንድሮ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የአስራ አንድ ድልድዮች ግንባታ አፈጻጻምም 70 ከመቶ መድረሱን ጠቅሰው በገጠር ተደራሽ መንገድ (URAP) ፕሮግራምም ከ136 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጻም የተሻለ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው "ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውም ጉልህ ነው" ብለዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026