
ሀዋሳ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ የሚደረገው ክትትልና ዕገዛ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።
ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች የክልል አመራሮች በፌደራልና በክልሉ መንግስት እየተገነቡ ያሉ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ተመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በክልሉ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው።
ፕሮጀክቶቹ በወቅቱ እንዲጠናቀቁ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው አሁናዊ አፈጻጸማቸው በተሻለ ደረጃ ላይ እንደሆነ አመልክተዋል።
የፌደራል መንግስት ባሳየው ቁርጠኝነትም የሀዌላ ቱላ-ውጅግራ-ያዬ-ወራንቻ የ85 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ግንባታ መጀመሩን ተናግረዋል ።
በአዲስ መልክ የተጀመረው የመንገዱ ግንባታ አፈጻጸም የተሻለ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸው በቀጣይም ተገቢው ክትትልና እገዛ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የጉብኝቱ ዓላማም የመንገድ መሰረተ ልማቶች ግንባታ በተያዘላቸው ጊዜ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲጀምሩ በማድረግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን አስታውቀዋል።
የክልሉ የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በበኩላቸው በክልሉ በርካታ የአዳዲስ መንገዶችና ድልድዮች ግንባታና ጥገና ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም 149 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 19 የመንገድ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የአፈር ስራ የሚከናወንባቸውን 10 የመንገድ ፕሮጀክቶችን በዘንድሮ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የአስራ አንድ ድልድዮች ግንባታ አፈጻጻምም 70 ከመቶ መድረሱን ጠቅሰው በገጠር ተደራሽ መንገድ (URAP) ፕሮግራምም ከ136 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጻም የተሻለ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው "ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውም ጉልህ ነው" ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026