የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በአፋር ክልል 15 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 62 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ ወስደዋል</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

ሰመራ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በግማሽ በጀት ዓመቱ 15 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 62 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ አስታወቁ።

እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የአስፈፃሚውን የስድስት ወራት የአፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት፣ በግማሽ ዓመቱ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።

በክልሉ የሚገኙ ለም መሬቶች ወደ ልማት እንዲገቡ በማድረግ ከለማው የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል።

በዚህም ከ20 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ መሰራጨቱን ጠቅሰው፤ ምርጥ ዘር ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የተሻለ ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።


የእንስሳት ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር ጤናቸውን መጠበቅ የሚያስችሉ ክትባቶች በስፋት መሰጠታቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ በግማሽ በጀት ዓመቱ 15 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 62 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።

ዋና ዋና የኢንቨስትመንት ዘርፎቹም ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ግንባታና ቱሪዝም መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢንቨስትመንት እድሉ 7 ሺህ 609 ለሚሆኑ ዜጎች ጊዜያዊ፣ 3 ሺህ 619 ለሚሆኑ ዜጎች ደግሞ ቋሚ የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልፀዋል።

በክልሉ በዳሊፋጊ ወረዳ፣ በሚሌና ሎጊያ ከተሞች ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መጀመራቸውን አስታውሰዋል።

የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሟላት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን 23 የተለያዩ ቦታዎች ላይ ውሃ ተደራሽ ለማድርግ ጥናት እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።

በክልሉ ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ወረዳዎች መጨመራቸውን በሪፖርታቸው የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ 29 ወረዳዎች መድረሳቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ሰላም ከመቸውም ጊዜ በላይ ሰፍኗል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ትጥቅ ይዘው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ከፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱ ተደርገው ወደ ሰላማዊ ህይወት መቀላቀላቸውን ገልፀዋል።

የሰላም ውይይቶችን በማዘጋጀትም የነበሩ ግጭቶች እንዲቀሩ ማድረግ የተቻለ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሰላም የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026