ሰመራ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በግማሽ በጀት ዓመቱ 15 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 62 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ አስታወቁ።
እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የአስፈፃሚውን የስድስት ወራት የአፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት፣ በግማሽ ዓመቱ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።
በክልሉ የሚገኙ ለም መሬቶች ወደ ልማት እንዲገቡ በማድረግ ከለማው የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል።
በዚህም ከ20 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ መሰራጨቱን ጠቅሰው፤ ምርጥ ዘር ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የተሻለ ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።
የእንስሳት ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር ጤናቸውን መጠበቅ የሚያስችሉ ክትባቶች በስፋት መሰጠታቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ በግማሽ በጀት ዓመቱ 15 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 62 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
ዋና ዋና የኢንቨስትመንት ዘርፎቹም ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ግንባታና ቱሪዝም መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኢንቨስትመንት እድሉ 7 ሺህ 609 ለሚሆኑ ዜጎች ጊዜያዊ፣ 3 ሺህ 619 ለሚሆኑ ዜጎች ደግሞ ቋሚ የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልፀዋል።
በክልሉ በዳሊፋጊ ወረዳ፣ በሚሌና ሎጊያ ከተሞች ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መጀመራቸውን አስታውሰዋል።
የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ለማሟላት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን 23 የተለያዩ ቦታዎች ላይ ውሃ ተደራሽ ለማድርግ ጥናት እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።
በክልሉ ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ወረዳዎች መጨመራቸውን በሪፖርታቸው የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ 29 ወረዳዎች መድረሳቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ ሰላም ከመቸውም ጊዜ በላይ ሰፍኗል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ትጥቅ ይዘው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ሃይሎች ከፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱ ተደርገው ወደ ሰላማዊ ህይወት መቀላቀላቸውን ገልፀዋል።
የሰላም ውይይቶችን በማዘጋጀትም የነበሩ ግጭቶች እንዲቀሩ ማድረግ የተቻለ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሰላም የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025