
አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፡- ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት መመዝገቡን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ የተቋሙን የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በዚህም እንደ ሀገር ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ኢትዮ ቴሌኮም ትልቁን ድርሻ ወስዶ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ለዕቅዱ ስኬታማነት ኢትዮ ቴሌኮም ለሶስት አመት የሚተገበር አምስት ግቦች ያሉት ስትራቴጂክ እቅድ ነድፎ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።
የአገልግሎት ጥራት፣ የገቢ ምንጭ ማስፋት፣ አዳዲስ የስራ እድል መፍጠር፣ ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት መስጠትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማጠናከር የስትራቴጂክ እቅዱ አካል መሆናቸውን አብራርተዋል።
በተለይም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን የሚያደርጉ የኔትወርክ ማስፋፊያዎችን መገንባትና የተቋማት አሰራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲደገፍ ማድረግ የእቅዱ ዋና ግቦች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪ የፋይናንስ ስርዓቱን ዲጂታላይዝ ማድረግና የዜጎችን መሰረታዊ እንቅስቃሴዎች የሚያቀሉ ቴክኖሎጂዎችን ማስረጽ የእቅዱ አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት አመቱ ስድስት ወራት 61 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን በመጥቀስ በቴሌ ብር አማካኝነት አንድ ትሪሊየን ብር ዝውውር መፈፀሙንም አክለዋል።

ወጪ ቆጣቢ የዲጂታል አገልግሎትን ተግባራዊ በማድረግ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ማዳን መቻሉን አስታውቀው ምጣኔው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ43 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን ገልጸዋል።
ተቋሙ ባለፉት ስድስት ወራት 202 በሚሆኑ አካባቢዎች አዳዲስ የገመድ አልባ አገልግሎቶች ማስፋቱን አንስተዋል።
ስምንት ከተሞችን የ5ኛ ትውልድ ወይም 5ጂ ኔትወርክ እንዲሁም 67 ከተሞችን የ4ኛ ትውልድ ወይም 4ጂ ኔትወርክ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን በመግለጫቸው አስታውቀዋል።
በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ አገልግሎት የተቋረጠባቸው አካባቢዎችን ዳግም ወደ አገልግሎት ለማስገባት በተሰራው ስራ 216 አካባቢዎች ሙሉ የቴሌኮም አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በመግለጫቸው አንስተዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026