የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በሲዳማ ክልል ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ።

በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ተግባራዊ በማድረግ ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዞንና የወረዳ አመራሮች የፓርቲውን የሰባት ወራት አፈጻጸም በሀዋሳ ገምግመዋል።

በመድረኩ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አብርሃም ማርሻሎ፤ በክልሉ ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በተለይም በለውጡ አመታት በሁሉም መስኮች የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል ለዜጎች ተጠቃሚነት እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ይከናወናሉ ነው ያሉት።

ክልሉ እምቅ የተፈጥሮ ሃብት የመልማት አቅምና ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆኑ መልካም እድሎች ያሉት በመሆኑ ባለሃብቶች በተለያዩ ዘርፎች እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

በሀገሪቱ ዋነኛ የእድገት መሰሶዎች ተብለው በተለዩት ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥሉ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በተለይም በግብርናው ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻልና ከተረጅነት ለመላቀቅ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ጥረቶች ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


በፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አስፋው ጎኔሶ፤ በፓርቲው የተቀመጡ የልማት ግቦች ያመጡትን ውጤት ለማስቀጠል በየደረጃው ያለው አመራር በቁርጠኝነት ለመፈፀም መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም “ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን እውን በማድረግ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025