የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በዕውቀትና ክህሎት የሚመራ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር ለአፍሪካውያን ብልጽግና መሰረት ነው - ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር)</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ በዕውቀትና ክህሎት የሚመራ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር ለአፍሪካውያን ብልጽግና መሰረት እንደሚሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) ገለጹ።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘላቂ የልማት ማዕከል ጋር በመተባበር በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ሰምምነት ላይ ያተኮረ ሙያዊ ውይይት አካሂዷል።

በዚሁ ጊዜ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር)፤ አፍሪካ የሚለማ ዕምቅ የተፈጥሮ ሃብትና የሰው ሃይል ጸጋ ያላት አህጉር ናት ብለዋል።

የአውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካና የእስያ አህጉራት ጠንካራ የመሰረተ ልማትና የንግድ ትስስር ለሀገራቱ ኢኮኖሚያዊ አቅም መጎልበት ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።


በአፍሪካም የህብረቱ መስራቾች የተለሙትን ግብ ተግባራዊ በማድረግ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ማሳለጥ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ለዚህም የመሰረተ ልማትና የንግድ ትስስር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካን አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

ሰላማዊት፣ የተረጋጋችና ብልጽግናዋን ያረጋገጠች አፍሪካን እውን ለማድረግም የመሪዎችን አጀንዳ ለማሳካት የአህጉሪቱ ምሁራንና የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የአህጉሪቱን ዜጎች በእውቀትና ክህሎት ለማጎልበት አፍሪካን በሁለንተናዊ መስክ ተቀራራቢና የጋራ ሥርዓተ ትምህርት ማልማት እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።

በትብብርና መተጋገዝ ላይ የተመሰረተ ጠንካራ አህጉራዊ የትምህርትና የምርምር ተቋማትን በመገንባት በዕውቀት የሚመራ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ስምምነትን መተግበር ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።


በአፍሪካ ልማት ባንክ የቀጣናዊ ውህደት ማስተባበሪያ ቢሮ ዳይሬክተር ጆይ ካቴጌከዋ(ዶ/ር) በበኩላቸው የምንመኛትን የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

ለዚህም የአፍሪካ ሀገራትን ህልም ማገናኘት ሚያስችል ጥራት ያለው የኢንዱስትሪ ምርት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታና ትብብር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትም የአህጉሪቱን ምርት እሴት በመጨመር ጥራት ያለው የኢንዱስትሪያላይዜሽን ሥርዓት ለመገንባት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የአፍሪካ ልማት ባንክም አህጉሪቱን በመሰረተ ልማትና በንግድ በሚያስተሳስሩ ተግባራት ላይ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ለነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ስኬት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ አንዷለም ጎሹ(ዶ/ር)፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት የውህደታችን ማፋጠኛ መንገድ በሚል ርዕስ የመነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል።

በጽሁፋቸውም የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት በአጀንዳ 2063 እውን ለማድረግ ከተቀመጡ መሰረታዊ ጉዳዮች መካከል እንዱና አስፈላጊው ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026