የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ሀዋሳ ከተማን ለቱሪዝምና ኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን ለቱሪዝምና ኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ በሀዋሳ ከተማ ለሚያስገነባው ሆቴል የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።


አቶ ደስታ በዚህ ወቅት እንደገለጹት የሃዋሳ ከተማን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተጀመሩ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

የሆቴል ኢንቨስትመንት መስፋፋት ሃይማኖታዊና ሀገራዊ በዓላትን ጨምሮ በርካታ ሁነቶችን ለምታስተናግደው ሀዋሳ ከተማ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለውም ገልጸዋል።

በመሆኑም ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ የጀመረው የሆቴል ግንባታ ከተማዋን ይበልጥ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንደሚያደርጋት ጠቅሰዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሁለተኛ ምዕራፍ ከሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ጋር በማስተሳሰር እንደሚከናወን ተናግረዋል።

ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎችን በማጠናከርና አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ለኑሮና ለመዝናናት ምቹ የማድረጉ ተግባር በትኩረት ይከናወናል ብለዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በበኩላቸው በከተማዋ ያለው ሰላም፣ የህዝቡ አንድነትና መሰረተ-ልማት ከተማዋን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓታል ብለዋል።

ለሃገር እድገት ጉልህ አሻራ እያሳረፈ ያለው ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በከተማዋ የጀመረው የሆቴልና ሪዞርት ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከተማ አስተዳደሩ ተገቢውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉም አረጋግጠዋል።

በሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሆቴሎችና ሪዞርቶች ክላስተር ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዘውዴ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ በሃገር እድገት ላይ ጉልህ ሚና ያለውን የልማት ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ዛሬ የግንባታ ሥራው የተጀመረው የ"ፎር ፖይንት ባይ ሸራተን ሀዋሳ ሪዞርት ሆቴል" በ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚከናወነው ግንባታ በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ አስታውቀዋል።

ሪዞርት ሆቴሉ በግንባታ ሂደት ለ500 ዜጎች፤ ግንባታው ተጠናቆ ወደ አገልግሎት ሲገባም ደግሞ ለ350 ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ይፈጠራል ብለዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የሲዳማ ክልልና የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመንግስት አመራሮች፣ የህብረሰተሰብ ተወካዮችና የንግዱ ማህበረሰብ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025