
አዳማ፤የካቲት 10/2017 (ኢዜአ).፦የዋጋ ግሽበትን የመቆጣጠርና የመረጃ ትንተና ስርአትን ማሻሻል እንደሚገባ ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከመላ ሀገሪቷ ለተውጣጡ የመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች በአዳማ ስልጠና ሰጥቷል።

በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍሰሐፅዮን፥ በኢኮኖሚ እድገትና ልማት ሂደት የዋጋ ግሽበት ቁጥጥርና ትንተና መረጃ አቅርቦትን ማሻሻል ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ የሚደረጉ ጥናቶች ለፖሊሲ ትልቅ ግብአት መሆናቸውን አንስተው፥ መረጃን በተሟላ መልኩ በጥራት መሰብሰብ እንደሚገባ እና የመረጃ ሰብሳቢዎች እውቀትና ክህሎት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
የገቢ ግብርን ከመወሰንና ሌሎችም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ተግባራትን ለማከናወን አስፈላጊነቱን አብራርተው በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር)፤ የችርቻሮ የዋጋ ጥናት ለፖሊሲ ቀረፃና ውሳኔ ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ለአገልግሎቱ በልዩ ትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም መረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ጥራት ያለው መረጃ ለመሰብሰብ በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአዳማ ከዛሬ ጀምሮ ለ20 ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የተውጣጡ 200 መረጃ ሰብሳቢዎች እና ተቆጣጣሪዎች እየተሳተፉ ነው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026