የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የዋጋ ግሽበትን የመቆጣጠርና የመረጃ ትንተና ስርአትን ማሻሻል ይገባል</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤የካቲት 10/2017 (ኢዜአ).፦የዋጋ ግሽበትን የመቆጣጠርና የመረጃ ትንተና ስርአትን ማሻሻል እንደሚገባ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከመላ ሀገሪቷ ለተውጣጡ የመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች በአዳማ ስልጠና ሰጥቷል።


በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍሰሐፅዮን፥ በኢኮኖሚ እድገትና ልማት ሂደት የዋጋ ግሽበት ቁጥጥርና ትንተና መረጃ አቅርቦትን ማሻሻል ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ የሚደረጉ ጥናቶች ለፖሊሲ ትልቅ ግብአት መሆናቸውን አንስተው፥ መረጃን በተሟላ መልኩ በጥራት መሰብሰብ እንደሚገባ እና የመረጃ ሰብሳቢዎች እውቀትና ክህሎት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

የገቢ ግብርን ከመወሰንና ሌሎችም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ተግባራትን ለማከናወን አስፈላጊነቱን አብራርተው በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል አመላክተዋል።


የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር)፤ የችርቻሮ የዋጋ ጥናት ለፖሊሲ ቀረፃና ውሳኔ ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ለአገልግሎቱ በልዩ ትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም መረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ጥራት ያለው መረጃ ለመሰብሰብ በከፍተኛ ኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በአዳማ ከዛሬ ጀምሮ ለ20 ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የተውጣጡ 200 መረጃ ሰብሳቢዎች እና ተቆጣጣሪዎች እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026