የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በትግራይ ክልል ያለው የማእድን ኃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

ሽሬ እንዳስላሴ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ህጋዊ ያልሆነ የማእድን ኃብት አመራረትና አጠቃቀምን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

የትግራይ ማእድን ኃብት ለዘላቂ ልማት፣ ዕድሎችና ተግዳሮቶቹ በሚል መሪ ሀሳብ አክሱም ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው አውደ ጥናት በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ተካሂዷል።


የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረ እየሱስ ብርሃነ በአውደ ጥናቱ ላይ እንዳሉት በክልሉ እየተስተዋለ ያለውን የተዛባ የማአድን ኃብት አጠቃቀም በመቅረፍ በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል በቅንጅት መስራት ይገባል ።

ህጋዊ ባልሆነ መንገድና ኃላፊነት በጎደለው አሰራር እየተከናወነ ባለው የማእድን ኃብት አጠቃቀም የተፈጥሮ ሃብቱ ለአገር እድገት ከመዋል ይልቅ ከፍተኛ ምዝበራ እየደረሰበት ነው ብለዋል።

እንዲሁም በሚደረገው ህገ ወጥ ፍለጋ በሰውና በእንስሳት ላይ ችግር እያስከተለ መሆኑን ተናግረዋል ።

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከምርምር ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።

በአውደ ጥናቱ ላይ በማእድን አጠቃቀም ዙሪያ በተለያዩ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025