
ሽሬ እንዳስላሴ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ህጋዊ ያልሆነ የማእድን ኃብት አመራረትና አጠቃቀምን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
የትግራይ ማእድን ኃብት ለዘላቂ ልማት፣ ዕድሎችና ተግዳሮቶቹ በሚል መሪ ሀሳብ አክሱም ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው አውደ ጥናት በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ተካሂዷል።

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረ እየሱስ ብርሃነ በአውደ ጥናቱ ላይ እንዳሉት በክልሉ እየተስተዋለ ያለውን የተዛባ የማአድን ኃብት አጠቃቀም በመቅረፍ በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል በቅንጅት መስራት ይገባል ።
ህጋዊ ባልሆነ መንገድና ኃላፊነት በጎደለው አሰራር እየተከናወነ ባለው የማእድን ኃብት አጠቃቀም የተፈጥሮ ሃብቱ ለአገር እድገት ከመዋል ይልቅ ከፍተኛ ምዝበራ እየደረሰበት ነው ብለዋል።
እንዲሁም በሚደረገው ህገ ወጥ ፍለጋ በሰውና በእንስሳት ላይ ችግር እያስከተለ መሆኑን ተናግረዋል ።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከምርምር ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።
በአውደ ጥናቱ ላይ በማእድን አጠቃቀም ዙሪያ በተለያዩ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026