
ሽሬ እንዳስላሴ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ህጋዊ ያልሆነ የማእድን ኃብት አመራረትና አጠቃቀምን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
የትግራይ ማእድን ኃብት ለዘላቂ ልማት፣ ዕድሎችና ተግዳሮቶቹ በሚል መሪ ሀሳብ አክሱም ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው አውደ ጥናት በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ተካሂዷል።

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረ እየሱስ ብርሃነ በአውደ ጥናቱ ላይ እንዳሉት በክልሉ እየተስተዋለ ያለውን የተዛባ የማአድን ኃብት አጠቃቀም በመቅረፍ በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል በቅንጅት መስራት ይገባል ።
ህጋዊ ባልሆነ መንገድና ኃላፊነት በጎደለው አሰራር እየተከናወነ ባለው የማእድን ኃብት አጠቃቀም የተፈጥሮ ሃብቱ ለአገር እድገት ከመዋል ይልቅ ከፍተኛ ምዝበራ እየደረሰበት ነው ብለዋል።
እንዲሁም በሚደረገው ህገ ወጥ ፍለጋ በሰውና በእንስሳት ላይ ችግር እያስከተለ መሆኑን ተናግረዋል ።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከምርምር ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።
በአውደ ጥናቱ ላይ በማእድን አጠቃቀም ዙሪያ በተለያዩ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026