
ሽሬ እንዳስላሴ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ህጋዊ ያልሆነ የማእድን ኃብት አመራረትና አጠቃቀምን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
የትግራይ ማእድን ኃብት ለዘላቂ ልማት፣ ዕድሎችና ተግዳሮቶቹ በሚል መሪ ሀሳብ አክሱም ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው አውደ ጥናት በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ተካሂዷል።

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረ እየሱስ ብርሃነ በአውደ ጥናቱ ላይ እንዳሉት በክልሉ እየተስተዋለ ያለውን የተዛባ የማአድን ኃብት አጠቃቀም በመቅረፍ በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል በቅንጅት መስራት ይገባል ።
ህጋዊ ባልሆነ መንገድና ኃላፊነት በጎደለው አሰራር እየተከናወነ ባለው የማእድን ኃብት አጠቃቀም የተፈጥሮ ሃብቱ ለአገር እድገት ከመዋል ይልቅ ከፍተኛ ምዝበራ እየደረሰበት ነው ብለዋል።
እንዲሁም በሚደረገው ህገ ወጥ ፍለጋ በሰውና በእንስሳት ላይ ችግር እያስከተለ መሆኑን ተናግረዋል ።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከምርምር ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።
በአውደ ጥናቱ ላይ በማእድን አጠቃቀም ዙሪያ በተለያዩ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026