
ጅማ፣የካቲት 11/2017 (ኢዜአ)፡- የጅማ ከተማን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግና አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የ"ሰማርት ሲቲ ፕሮጀክት" የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ።
ስምምነቱ የተፈረመው በኢትዮ ቴሌኮምና በጅማ ከተማ አስተዳደር መካከል ነው።
በትናንትናው እለት በጅማ ከተማ አምስተኛው ትውልድን ሞባይል ኔትወርክ (5G) ያስተዋወቀው ኢትዮ- ቴሌኮም ዛሬ ደግሞ ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ መስማማቱን ገልጿል።

ፕሮጀክቱ የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎት አሰጣጥ ያሳልጣል፣ መረጃ አስተዳደርን ያቀላጥፋል፣ ደህንነትና ትራንስፖርትን ዘርፉን ለማሻሻልም ያግዛል ተብሏል።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፤ የጅማ ከተማን ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ኩባንያው የሚጠበቅበትን ይወጣል ብለዋል።
ኢትዮ-ቴሌኮም የተቀናጀ የቴሌኮምና የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን መሰረተ ልማትን ለማቅረብ እንደሚሰራም አመልክተዋል።
የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በበኩላቸው ከተማዋን 'ስማርት ሲቲ' ለማድረግ ስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል።
ጅማ ከተማ የተሻለ መሰረተ ልማት ያላት፣ ሰላምና ደህንነቷ የተረጋገጠ ትሆን ዘንድ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ተገቢነት ያለው መሆኑንም እንሰተዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026