
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ በዓለም የንግድ ምሕዳር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት የኢትዮጵያ የንግድ ምልክቶችና ብራንዶች የሕግ ጥበቃ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ገለፀ፡፡
ባለስልጣኑ በዘርፉ ላይ ግልጽነት ለመፍጠር ያለመ የብራንድ አምባሳደሮችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄዷል፡፡
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳሉ ሞሲሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ባለስልጣኑ አዕምሯዊ ንብረት ስርዓትን የመምራት እና ዘርፉ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት የሚጠበቅበትን ሚና እንዲጫወት የማድረግ ስራ እያከናወነ ነው።

የአዕምሯዊ ንብረት፣ የንግድ ምልክትና ብራንድ፣ የስነ ጥበብና ኪነ ጥበብ ውጤት ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የመመዝገብ፣ የማስተዋወቅ፣ ህጋዊ ጥበቃ እንዲያገኙ የማስቻል ስራ እየሰራ ነውም ብለዋል፡፡
የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ጠንካራ ጥበቃ እንዲያገኙ የወጡ ሕጎች ተፈጻሚ በማድረግ አበረታች ስራዎች ቢከናወኑም ከሀገሪቷ ህዝብ ቁጥር፣ ከአገልግሎትና ምርት ብዛት አኳያ ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ጨምሮ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ንግድ ምሕዳር ውስጥ እየገባች መሆኑን አስታውሰዋል።
በዚህም በዓለም የንግድ ምሕዳር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ንግድ ምልክቶችና ብራንዶች የሕግ ጥበቃ ማግኘት እንደሚጠበቅ አንስተዋል።
በባለስልጣኑ የንግድ ምልክት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ትዕግስት ቦጋለ በበኩላቸው፤ የንግድ ምልክቶች ልዩ፣ የማህበረሰቡን እሴት የማይነኩና የፈጠራ ሀሳብ የታከለበት መሆን እንዳለባቸው ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ 33 ሺህ ገዳማ የንግድ ምልክቶችመኖራቸውን ጠቅሰው፤ 18 ሺህ የሚሆኑት የሀገር እንደሆኑ ገልጸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026