
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ በዓለም የንግድ ምሕዳር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት የኢትዮጵያ የንግድ ምልክቶችና ብራንዶች የሕግ ጥበቃ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ገለፀ፡፡
ባለስልጣኑ በዘርፉ ላይ ግልጽነት ለመፍጠር ያለመ የብራንድ አምባሳደሮችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄዷል፡፡
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳሉ ሞሲሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ባለስልጣኑ አዕምሯዊ ንብረት ስርዓትን የመምራት እና ዘርፉ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት የሚጠበቅበትን ሚና እንዲጫወት የማድረግ ስራ እያከናወነ ነው።

የአዕምሯዊ ንብረት፣ የንግድ ምልክትና ብራንድ፣ የስነ ጥበብና ኪነ ጥበብ ውጤት ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የመመዝገብ፣ የማስተዋወቅ፣ ህጋዊ ጥበቃ እንዲያገኙ የማስቻል ስራ እየሰራ ነውም ብለዋል፡፡
የአዕምሯዊ ንብረት መብቶች ጠንካራ ጥበቃ እንዲያገኙ የወጡ ሕጎች ተፈጻሚ በማድረግ አበረታች ስራዎች ቢከናወኑም ከሀገሪቷ ህዝብ ቁጥር፣ ከአገልግሎትና ምርት ብዛት አኳያ ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ጨምሮ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ንግድ ምሕዳር ውስጥ እየገባች መሆኑን አስታውሰዋል።
በዚህም በዓለም የንግድ ምሕዳር ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ንግድ ምልክቶችና ብራንዶች የሕግ ጥበቃ ማግኘት እንደሚጠበቅ አንስተዋል።
በባለስልጣኑ የንግድ ምልክት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ትዕግስት ቦጋለ በበኩላቸው፤ የንግድ ምልክቶች ልዩ፣ የማህበረሰቡን እሴት የማይነኩና የፈጠራ ሀሳብ የታከለበት መሆን እንዳለባቸው ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ 33 ሺህ ገዳማ የንግድ ምልክቶችመኖራቸውን ጠቅሰው፤ 18 ሺህ የሚሆኑት የሀገር እንደሆኑ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026