
ካራ-ቆርጮ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገሪቱ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ ሀይል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡
አገልግሎቱ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ጋር በመተባበር በደቡበ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ''ካራ-ቆርጮ'' እና ''ካራ-ዱስ'' ቀበሌዎች 425 ኪሎ ዋት የሚያመነጩ የሶላር ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።
የአገልግሎቱ ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ክንፈ ነጋሽ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት ተቋሙ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ እየሰራ ነው፡፡
በተለይ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀት ላይ የሚገኙ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዚህ የሀይል አቅርቦትም ከ240 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ እየተሰራ መሆኑን አቶ ክንፈ አመልክተዋል፡፡
በደቡብ ኦሞ ዞን ''ካራ-ቆርጮ'' እና ''ካራ-ዱስ'' ቀበሌዎች የተመረቁት የሶላር ፕሮጀክቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።

ፕሮጀክቶቹ 425 ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ከ6 ሺህ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በበኩላቸው የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በሃገሪቱ በየዘርፉ እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ተከትሎ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት መጨመሩን ጠቁመዋል
በደቡብ ኦሞ ዞን ከሚገኙ 185 በላይ ቀበሌዎች አብዛኞቹ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንደማያገኙ የገለጹት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ናቸው፡፡
የሀይል እቅርቦት እጥረት ፈተና ሆኖ መቆየቱን ያስታወሱት አስተዳዳሪው፣ በሐመር ወረዳ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር በርቀት ላይ ለሚገኙ ቀበሌዎች ከፀሐይ የኃይል አማራጭ እንዲያገኙ የተጀመረው ሥራ ስራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የአካባቢው አርብቶ አደሮች በአካባቢው የኤሌክትሪክ ሀይል ባለመኖሩ በጨለማ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸዋል።
"አሁን ከጨለማ ወደ ብርሃን ተሸጋግረናል" ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ነው የተናገሩት፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026