የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በሀገሪቱ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ ሀይል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው  </p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ካራ-ቆርጮ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገሪቱ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ ሀይል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ጋር በመተባበር በደቡበ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ''ካራ-ቆርጮ'' እና ''ካራ-ዱስ'' ቀበሌዎች 425 ኪሎ ዋት የሚያመነጩ የሶላር ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።

የአገልግሎቱ ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ክንፈ ነጋሽ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት ተቋሙ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ እየሰራ ነው፡፡

በተለይ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀት ላይ የሚገኙ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህ የሀይል አቅርቦትም ከ240 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ እየተሰራ መሆኑን አቶ ክንፈ አመልክተዋል፡፡

በደቡብ ኦሞ ዞን ''ካራ-ቆርጮ'' እና ''ካራ-ዱስ'' ቀበሌዎች የተመረቁት የሶላር ፕሮጀክቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።


ፕሮጀክቶቹ 425 ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ከ6 ሺህ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በበኩላቸው የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በሃገሪቱ በየዘርፉ እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ተከትሎ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት መጨመሩን ጠቁመዋል

በደቡብ ኦሞ ዞን ከሚገኙ 185 በላይ ቀበሌዎች አብዛኞቹ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንደማያገኙ የገለጹት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ናቸው፡፡

የሀይል እቅርቦት እጥረት ፈተና ሆኖ መቆየቱን ያስታወሱት አስተዳዳሪው፣ በሐመር ወረዳ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር በርቀት ላይ ለሚገኙ ቀበሌዎች ከፀሐይ የኃይል አማራጭ እንዲያገኙ የተጀመረው ሥራ ስራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።

ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የአካባቢው አርብቶ አደሮች በአካባቢው የኤሌክትሪክ ሀይል ባለመኖሩ በጨለማ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸዋል።

"አሁን ከጨለማ ወደ ብርሃን ተሸጋግረናል" ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026