የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በሀገሪቱ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ ሀይል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው  </p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ካራ-ቆርጮ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገሪቱ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ ሀይል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ጋር በመተባበር በደቡበ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ''ካራ-ቆርጮ'' እና ''ካራ-ዱስ'' ቀበሌዎች 425 ኪሎ ዋት የሚያመነጩ የሶላር ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።

የአገልግሎቱ ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ክንፈ ነጋሽ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት ተቋሙ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ እየሰራ ነው፡፡

በተለይ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀት ላይ የሚገኙ ከ230 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ከፀሐይ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህ የሀይል አቅርቦትም ከ240 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ እየተሰራ መሆኑን አቶ ክንፈ አመልክተዋል፡፡

በደቡብ ኦሞ ዞን ''ካራ-ቆርጮ'' እና ''ካራ-ዱስ'' ቀበሌዎች የተመረቁት የሶላር ፕሮጀክቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።


ፕሮጀክቶቹ 425 ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ከ6 ሺህ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በበኩላቸው የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በሃገሪቱ በየዘርፉ እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ተከትሎ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት መጨመሩን ጠቁመዋል

በደቡብ ኦሞ ዞን ከሚገኙ 185 በላይ ቀበሌዎች አብዛኞቹ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንደማያገኙ የገለጹት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ናቸው፡፡

የሀይል እቅርቦት እጥረት ፈተና ሆኖ መቆየቱን ያስታወሱት አስተዳዳሪው፣ በሐመር ወረዳ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር በርቀት ላይ ለሚገኙ ቀበሌዎች ከፀሐይ የኃይል አማራጭ እንዲያገኙ የተጀመረው ሥራ ስራ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።

ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ የአካባቢው አርብቶ አደሮች በአካባቢው የኤሌክትሪክ ሀይል ባለመኖሩ በጨለማ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸዋል።

"አሁን ከጨለማ ወደ ብርሃን ተሸጋግረናል" ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026