
አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡- ተቋማት የምርትና አገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ለሀገሪቱ እድገት የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ገለጸ፡፡
ድርጅቱ "በልህቀት ሞዴል አማካኝነት የጥራት ባሕልን ማሳደግ" በሚል መሪ ሃሳብ 3ኛውን ዙር የልህቀት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሂዷል፡፡
በውይይቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር)፣ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ቴዎድሮስ መብራት፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ድርጅቱ በ2000 ዓ.ም ሲመሰረት ለጥራት ልዩ ትኩረት የሚሰጥ የሽልማት ስርዓት በመዘርጋት የሀገሪቱን አለም አቀፍ የተወዳዳሪነት ብቃት ማሳደግ እና የጥራት ጽንሰ ሐሳብን በማስረጽ ጥራት የሀገሪቱ ባህል እንዲሆን ማገዝን ዓላማ በማድረግ ነው።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንትና የድርጅቱ የቦርድ ሰብሳቢ፤ ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) መድረኩ ድርጅቶች በጥራት የተሻለ አፈጻጸም ካሳዩ ድርጅቶች ልምድና ተሞክሮን የሚወስዱበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ድርጅቱ በተለይም ተቋማት ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራር በመከተል ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ ለሀገር አድገት አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ተቋማትም ምርትና አገልግሎታቸውን ቀልጣፋና ዘመናዊ በማድረግ ከሀገር ባለፈ ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን መስራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡
የተለያዩ ተቋማት ሃላፊዎች በበኩላቸው ፤ውይይቱ በቀጣይ ለተሻለ ምርትና አገልግሎት እንዲዘጋጁ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተለይም አሰራራቸውን ይበልጥ በማዘመን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ ቴዎድሮስ መብራት በበኩላቸው፤ ውይይቱ ከልምድ ልውውጥ በተጨማሪ የዘርፉ ምሁራን ስለጥራትና ልህቀት የጥናት ግኝቶቻቸውን ያቀረቡበት፣ ድርጅቶች የእርስ በእርስ ግንኙነት የፈጥሩበት፣ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026