አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ለአካባቢ ጥበቃ ስራ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፍጻሚ ፍስሃ ይትገሱ(ዶ/ር) አስታወቁ።
ለአካባቢጥበቃና ለጥራት በመጠንቀቅ የሚከናወን ምርት በዓለም ገበያ ተፈላጊ ነው ሲሉ የእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ጋር በሐዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ተገናኝተው በመከሩበት ወቅት እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ የሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ለአካባቢ ጥበቃ ስራ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው ይሰራሉ ።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከሚያስተዳድራቸው ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ 10ሩ ወደ ልዮ የኢኮኖሚ ዞን አደጉ
በእያንዳንዱ ዞን ውስጥ ለአካባቢ ብክለት ምክንያት የሚሆኑ የፋብሪካ ፍሳሾችን የሚያጣሩ የፍሳሽ ማጣሪ ጣቢያዎች (Zero Liquid Discharge) ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ በበኩላቸው በእስያ የሰራተኞች ደሞዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የአልባሳት እና ጨርቃጨርቅ አምራቾች የአፍሪካ ገበያን እዲያማትሩ እያስገደደ መሆኑን ገልጸዌል።
ይህ ሁኔታ ለኢትዮጵያ አልባሳት እና ጨርቃጨርቅ አምራቾች መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልጸው ሀገራቸው የእንግሊዝ ገዢዎችን ከኢትዮጵያ አምራቾች ጋር ለማስተሳሰር ጥረት እያደረገች መሆኗን መግለጻቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑን የስራ አንቅስቃሴ ተዘዋወረው በመመልከትም በኢትዮጵያ ያለውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማጠናከር በእንግሊዝ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላትን ከእንግሊዝ ባለሀብቶቸ ጋር በማስተሳሰር ሊሰራ የሚችልበትን አጋጣሚ ማየት እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ጋር በሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት ጠቁመው የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ ጉብኝትም ይሄንን ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር መግለጻቸው ይታወሳል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025