
አዲስ አበባ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያና እንግሊዝ ዘመን ተሻጋሪ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚክ ዲፕሎማሲ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአገሪቷ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ አንጄላ ሬይነር በእንግሊዝ መንግስት የውጭ የጋራ ልማት ቢሮ (FCDO) የተገዙ 12 አንቡላንሶችን ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል።
በልማት ቢሮው የተበረከቱ አንቡላንሶችን ቁልፍም የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር እጅ ተረክበዋል።

እነዚህ አዳዲስ አንቡላንሶችም ለእናቶችና ህፃናት ፈጣንና የተሻለ የጤና ሰብዓዊ አገልግሎት በመስጠት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውና የተሟላ የህክምና ቁሳቁስ የታጠቁ መሆናቸው ተገልጿል።
በዚሁ ጊዜ የእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር፤ በኢትዮጵያና እንግሊዝ መካከል በንግድ፣ በኢኮኖሚ፣ በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ትብብራቸው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ቆይታቸውም አገሪቷ የሚያጋጥሟትን ጫናዎች በመቋቋም ዕድገቷን ማስቀጠል የምትችል መሆኗን እንደተገነዘቡ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እና በእንግሊዝ መካከል ካሉ ግዙፍ የሁለትዮሽ ፕሮጀክቶች መካከል የሰብዓዊ ድጋፍና ትብብር ፕሮጀክት ትልቁ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ቆይታቸውም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር በኢትዮ-እንግሊዝ የጋራ የብልጽግና ርዕይና ፍላጎት ላይ ገንቢ ምክክር ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይም እንግሊዝ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘርፈ ብዙ ትብብር በማስቀጠል ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስራ ሁለት አንቡላንሶችን ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ፤ የእንግሊዝ መንግስት ለጤና አገልግሎት የሚውሉ አንቡላንሶችን በማበርከቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የተደረገው ድጋፍም ቅጽበታዊ አደጋዎችን ምላሽ ለመስጠት በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ማሰልጠኛ ማዕከል በተደረገው የርክክብ ሥነ-ስርዓት የማኅበሩ የስራ ኃላፊዎች እና በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር አላስቴር ማክፌል ተገኝተዋል።
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር የተመራው ልዑክም በማኅበሩ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት በቀጣይ የትብብር መስኮች ከማኅበሩ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይቷል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026