
አዲስ አበባ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያና እንግሊዝ ዘመን ተሻጋሪ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚክ ዲፕሎማሲ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአገሪቷ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ አንጄላ ሬይነር በእንግሊዝ መንግስት የውጭ የጋራ ልማት ቢሮ (FCDO) የተገዙ 12 አንቡላንሶችን ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል።
በልማት ቢሮው የተበረከቱ አንቡላንሶችን ቁልፍም የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር እጅ ተረክበዋል።

እነዚህ አዳዲስ አንቡላንሶችም ለእናቶችና ህፃናት ፈጣንና የተሻለ የጤና ሰብዓዊ አገልግሎት በመስጠት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውና የተሟላ የህክምና ቁሳቁስ የታጠቁ መሆናቸው ተገልጿል።
በዚሁ ጊዜ የእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር፤ በኢትዮጵያና እንግሊዝ መካከል በንግድ፣ በኢኮኖሚ፣ በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ትብብራቸው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ቆይታቸውም አገሪቷ የሚያጋጥሟትን ጫናዎች በመቋቋም ዕድገቷን ማስቀጠል የምትችል መሆኗን እንደተገነዘቡ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እና በእንግሊዝ መካከል ካሉ ግዙፍ የሁለትዮሽ ፕሮጀክቶች መካከል የሰብዓዊ ድጋፍና ትብብር ፕሮጀክት ትልቁ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ቆይታቸውም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር በኢትዮ-እንግሊዝ የጋራ የብልጽግና ርዕይና ፍላጎት ላይ ገንቢ ምክክር ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይም እንግሊዝ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዘርፈ ብዙ ትብብር በማስቀጠል ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስራ ሁለት አንቡላንሶችን ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ፤ የእንግሊዝ መንግስት ለጤና አገልግሎት የሚውሉ አንቡላንሶችን በማበርከቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የተደረገው ድጋፍም ቅጽበታዊ አደጋዎችን ምላሽ ለመስጠት በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ማሰልጠኛ ማዕከል በተደረገው የርክክብ ሥነ-ስርዓት የማኅበሩ የስራ ኃላፊዎች እና በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር አላስቴር ማክፌል ተገኝተዋል።
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር የተመራው ልዑክም በማኅበሩ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት በቀጣይ የትብብር መስኮች ከማኅበሩ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይቷል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026