
ድሬዳዋ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፦ ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ተወዳዳሪ መሆን የሚቻላው ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማከናወን እና መተግበር እንደሚጠይቅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ገለጹ።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ 10ኛው ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ "በፈጠራ የተደገፈ የምርምር ውጤት ለዘላቂ ዕድገት" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ነው።
ለሁለት ቀናት በተሰናዳው የምርምር ጉባዔ ላይ በተለያዩ ዘርፎች የተደረጉ ምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይካሄድባቸዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዑባህ አደም (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ለአገርንና ለህዝብ የሚበጁ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማካሄድ ይጠበቅባቸዋል።

ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምሮች ነባራዊ ዓለም ያገናዘቡና ችግር ፈቺ መሆን እንዳለባቸው ገልጸው፤ ጉባዔው ይህን ለማጠናከርና አገራዊ ትልሞችን ስኬታማ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ታፈሰ አስራት (ዶ/ር) በበኩላቸው በተለዋዋጭ ዓለም ላይ ተወዳዳሪ መሆን የሚቻለው ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምሮች በጥራት ማከናወንና መተግበር ሲቻል ነው ብለዋል።

የጥናትና ምርምር ውጤቶችን በተቀናጀ መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል ለዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና መሠረታዊ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በየዘርፉ የሚካሄዱ ምርምሮች የአገርን ዘላቂ ጥቅሞች እና ከፍታ በሚያረጋግጡ መንገድ በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ማድረግ እንደሚገባ ደግሞ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤና ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ነጋ አስራት (ፕሮፌሰር) ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ክስተቶችን እያስተናገገድ በመሆኑ ነባራዊ ሁኔታውን የዋጀና በፈጠራ የተደገፈ ጥናትና ምርምር በስፋትና በጥራት ማከናወን እንደሚሻ ገልጸዋል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ተማም አወል (ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የሚካሄዱ ጉባዔዎች ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመለወጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ጥሩ መደላደል መፍጠሩን ተናግረዋል።
በጉባዔው ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች በየዘርፉ የተከናወኑ 20 የጥናትና ምርምር ውጤቶች ለውይይት እየቀረቡ ናቸው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026