የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማውጣት እና መተግበር ይጠይቃል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፦ ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ተወዳዳሪ መሆን የሚቻላው ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማከናወን እና መተግበር እንደሚጠይቅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ገለጹ።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ 10ኛው ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ "በፈጠራ የተደገፈ የምርምር ውጤት ለዘላቂ ዕድገት" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ነው።

ለሁለት ቀናት በተሰናዳው የምርምር ጉባዔ ላይ በተለያዩ ዘርፎች የተደረጉ ምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይካሄድባቸዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዑባህ አደም (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ለአገርንና ለህዝብ የሚበጁ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማካሄድ ይጠበቅባቸዋል።

ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምሮች ነባራዊ ዓለም ያገናዘቡና ችግር ፈቺ መሆን እንዳለባቸው ገልጸው፤ ጉባዔው ይህን ለማጠናከርና አገራዊ ትልሞችን ስኬታማ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ታፈሰ አስራት (ዶ/ር) በበኩላቸው በተለዋዋጭ ዓለም ላይ ተወዳዳሪ መሆን የሚቻለው ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምሮች በጥራት ማከናወንና መተግበር ሲቻል ነው ብለዋል።

የጥናትና ምርምር ውጤቶችን በተቀናጀ መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል ለዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና መሠረታዊ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በየዘርፉ የሚካሄዱ ምርምሮች የአገርን ዘላቂ ጥቅሞች እና ከፍታ በሚያረጋግጡ መንገድ በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ማድረግ እንደሚገባ ደግሞ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤና ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ነጋ አስራት (ፕሮፌሰር) ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ክስተቶችን እያስተናገገድ በመሆኑ ነባራዊ ሁኔታውን የዋጀና በፈጠራ የተደገፈ ጥናትና ምርምር በስፋትና በጥራት ማከናወን እንደሚሻ ገልጸዋል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ተማም አወል (ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የሚካሄዱ ጉባዔዎች ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመለወጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ጥሩ መደላደል መፍጠሩን ተናግረዋል።

በጉባዔው ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች በየዘርፉ የተከናወኑ 20 የጥናትና ምርምር ውጤቶች ለውይይት እየቀረቡ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026