
ድሬዳዋ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፦ ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ተወዳዳሪ መሆን የሚቻላው ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማከናወን እና መተግበር እንደሚጠይቅ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ገለጹ።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ 10ኛው ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ "በፈጠራ የተደገፈ የምርምር ውጤት ለዘላቂ ዕድገት" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ነው።
ለሁለት ቀናት በተሰናዳው የምርምር ጉባዔ ላይ በተለያዩ ዘርፎች የተደረጉ ምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይካሄድባቸዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዑባህ አደም (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ለአገርንና ለህዝብ የሚበጁ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን ማካሄድ ይጠበቅባቸዋል።

ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምሮች ነባራዊ ዓለም ያገናዘቡና ችግር ፈቺ መሆን እንዳለባቸው ገልጸው፤ ጉባዔው ይህን ለማጠናከርና አገራዊ ትልሞችን ስኬታማ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ታፈሰ አስራት (ዶ/ር) በበኩላቸው በተለዋዋጭ ዓለም ላይ ተወዳዳሪ መሆን የሚቻለው ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምሮች በጥራት ማከናወንና መተግበር ሲቻል ነው ብለዋል።

የጥናትና ምርምር ውጤቶችን በተቀናጀ መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል ለዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና መሠረታዊ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በየዘርፉ የሚካሄዱ ምርምሮች የአገርን ዘላቂ ጥቅሞች እና ከፍታ በሚያረጋግጡ መንገድ በተቀናጀ መንገድ እንዲተገበሩ ማድረግ እንደሚገባ ደግሞ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤና ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ነጋ አስራት (ፕሮፌሰር) ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ተለዋዋጭ ክስተቶችን እያስተናገገድ በመሆኑ ነባራዊ ሁኔታውን የዋጀና በፈጠራ የተደገፈ ጥናትና ምርምር በስፋትና በጥራት ማከናወን እንደሚሻ ገልጸዋል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ተማም አወል (ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የሚካሄዱ ጉባዔዎች ችግር ፈቺ ምርምሮችን ወደ ተግባር ለመለወጥና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ጥሩ መደላደል መፍጠሩን ተናግረዋል።
በጉባዔው ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች በየዘርፉ የተከናወኑ 20 የጥናትና ምርምር ውጤቶች ለውይይት እየቀረቡ ናቸው።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026