የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ለጎንደር ኮሪደር ልማት ነዋሪው ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል- ከተማው አስተዳደሩ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡- የጎንደር ነዋሪዎች ለከተማዋ የኮሪደር ልማት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የፌደራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የጎንደር ከተማ የግማሽ በጀት ዓመቱ የኮሪደር የልማት ስራዎችን የሚገመግም የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂደዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማውን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን አነቃቅቷል።

የከተማዋ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማቱ በራሳቸው ተነሳሽነት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማበርከታቸውን አስታውቀዋል።

በተጨማሪም የጉልበትና የሙያ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል።

ኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በተቀናጀ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በስራ ባህልን አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለማየሁ አየለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጎንደር ኮሪደር ልማት አፈጻጸም ሌሎች ከተሞች ጭምር መልካም ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።

የአዘዞ ጎንደር የኮንክሪት አስፋልት መንገድን ህብረተሰቡ በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብና በመጠበቅ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጸጋዬ ሞሼ ፤ የኮሪደር ልማቱ ጎንደር ታሪኳን በሚመጥን ልክ እንድትለማ እድል የፈጠረና ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ የልማት ስራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በከተማው ባለፋት ስድስት ወራት ታቅደው የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች አበረታች እንደሆኑ መገንዘባቸው የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሙዐዝ በድሩ(ዶ/ር) ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026