
ጎንደር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡- የጎንደር ነዋሪዎች ለከተማዋ የኮሪደር ልማት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የፌደራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የጎንደር ከተማ የግማሽ በጀት ዓመቱ የኮሪደር የልማት ስራዎችን የሚገመግም የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂደዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማውን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን አነቃቅቷል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማቱ በራሳቸው ተነሳሽነት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማበርከታቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የጉልበትና የሙያ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል።
ኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በተቀናጀ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በስራ ባህልን አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለማየሁ አየለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጎንደር ኮሪደር ልማት አፈጻጸም ሌሎች ከተሞች ጭምር መልካም ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።
የአዘዞ ጎንደር የኮንክሪት አስፋልት መንገድን ህብረተሰቡ በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብና በመጠበቅ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።
በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጸጋዬ ሞሼ ፤ የኮሪደር ልማቱ ጎንደር ታሪኳን በሚመጥን ልክ እንድትለማ እድል የፈጠረና ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ የልማት ስራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በከተማው ባለፋት ስድስት ወራት ታቅደው የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች አበረታች እንደሆኑ መገንዘባቸው የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሙዐዝ በድሩ(ዶ/ር) ናቸው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026