
ጎንደር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡- የጎንደር ነዋሪዎች ለከተማዋ የኮሪደር ልማት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የፌደራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የጎንደር ከተማ የግማሽ በጀት ዓመቱ የኮሪደር የልማት ስራዎችን የሚገመግም የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂደዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማውን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን አነቃቅቷል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማቱ በራሳቸው ተነሳሽነት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማበርከታቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የጉልበትና የሙያ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል።
ኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በተቀናጀ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በስራ ባህልን አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለማየሁ አየለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጎንደር ኮሪደር ልማት አፈጻጸም ሌሎች ከተሞች ጭምር መልካም ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።
የአዘዞ ጎንደር የኮንክሪት አስፋልት መንገድን ህብረተሰቡ በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብና በመጠበቅ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።
በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጸጋዬ ሞሼ ፤ የኮሪደር ልማቱ ጎንደር ታሪኳን በሚመጥን ልክ እንድትለማ እድል የፈጠረና ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ የልማት ስራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በከተማው ባለፋት ስድስት ወራት ታቅደው የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች አበረታች እንደሆኑ መገንዘባቸው የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሙዐዝ በድሩ(ዶ/ር) ናቸው።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026