የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ለጎንደር ኮሪደር ልማት ነዋሪው ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል- ከተማው አስተዳደሩ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡- የጎንደር ነዋሪዎች ለከተማዋ የኮሪደር ልማት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የፌደራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የጎንደር ከተማ የግማሽ በጀት ዓመቱ የኮሪደር የልማት ስራዎችን የሚገመግም የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂደዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማውን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን አነቃቅቷል።

የከተማዋ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማቱ በራሳቸው ተነሳሽነት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማበርከታቸውን አስታውቀዋል።

በተጨማሪም የጉልበትና የሙያ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል።

ኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በተቀናጀ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በስራ ባህልን አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለማየሁ አየለ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጎንደር ኮሪደር ልማት አፈጻጸም ሌሎች ከተሞች ጭምር መልካም ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።

የአዘዞ ጎንደር የኮንክሪት አስፋልት መንገድን ህብረተሰቡ በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብና በመጠበቅ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጸጋዬ ሞሼ ፤ የኮሪደር ልማቱ ጎንደር ታሪኳን በሚመጥን ልክ እንድትለማ እድል የፈጠረና ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ የልማት ስራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በከተማው ባለፋት ስድስት ወራት ታቅደው የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች አበረታች እንደሆኑ መገንዘባቸው የተናገሩት ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሙዐዝ በድሩ(ዶ/ር) ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026