የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በከተማ አስተዳደሩ የተገነባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ ተመርቆ ስራ ጀመረ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስገነባው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ እንደገለጹት በመዲናዋ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ ሃይል መሙላት የሚያችሉ ጣቢያዎችን የማስፋፋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።


ከተማ አስተዳደሩ ያስገነባው ይህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ መሙያ ጣቢያ በአንድ ጊዜ 16 ተሽከርካሪዎችን ሃይል መሙላት እንደሚያስችል ገልፀው እንደመኪኖቹ አይነት ሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ከ20 እስከ 45 ደቂቃ እንደሚወስድም ጠቁመዋል።

የከባቢ አየር ብክለትን ለመከላከል እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም ጠቅሰዋል።

ታዳሽ ሀይልን ከማስፋትና የአካባቢ ብክለትን ከመቀነስ አንፃር አስተዋፅኦ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ተጠቃሚነት ለማስፋት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል።


ጣቢያው በውስጡ 1ሺህ ሰዎችን መያዝ የሚችል ሲኒማቲክ ስክሪን የተገጠመለት አንፊ ቲያትር፣ 2 የህዝብ መዝናኛ ካፍቴሪያዎች እና የህጻናት ማቆያ እንዳሉትም ገልጸዋል።

እንዲሁም 800 ኪሎ ዋት ያለው ዝግጁ ጄኔሬተር ያለው ሲሆን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የተደገፈ የሴኪዩሪቲ ሲስተም እንደተገጠመለትም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025