የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>በከተማ አስተዳደሩ የተገነባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ ተመርቆ ስራ ጀመረ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስገነባው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ እንደገለጹት በመዲናዋ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ ሃይል መሙላት የሚያችሉ ጣቢያዎችን የማስፋፋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።


ከተማ አስተዳደሩ ያስገነባው ይህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ መሙያ ጣቢያ በአንድ ጊዜ 16 ተሽከርካሪዎችን ሃይል መሙላት እንደሚያስችል ገልፀው እንደመኪኖቹ አይነት ሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ከ20 እስከ 45 ደቂቃ እንደሚወስድም ጠቁመዋል።

የከባቢ አየር ብክለትን ለመከላከል እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም ጠቅሰዋል።

ታዳሽ ሀይልን ከማስፋትና የአካባቢ ብክለትን ከመቀነስ አንፃር አስተዋፅኦ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ተጠቃሚነት ለማስፋት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል።


ጣቢያው በውስጡ 1ሺህ ሰዎችን መያዝ የሚችል ሲኒማቲክ ስክሪን የተገጠመለት አንፊ ቲያትር፣ 2 የህዝብ መዝናኛ ካፍቴሪያዎች እና የህጻናት ማቆያ እንዳሉትም ገልጸዋል።

እንዲሁም 800 ኪሎ ዋት ያለው ዝግጁ ጄኔሬተር ያለው ሲሆን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የተደገፈ የሴኪዩሪቲ ሲስተም እንደተገጠመለትም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026