
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስገነባው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ እንደገለጹት በመዲናዋ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ ሃይል መሙላት የሚያችሉ ጣቢያዎችን የማስፋፋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

ከተማ አስተዳደሩ ያስገነባው ይህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ መሙያ ጣቢያ በአንድ ጊዜ 16 ተሽከርካሪዎችን ሃይል መሙላት እንደሚያስችል ገልፀው እንደመኪኖቹ አይነት ሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ከ20 እስከ 45 ደቂቃ እንደሚወስድም ጠቁመዋል።
የከባቢ አየር ብክለትን ለመከላከል እና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም ጠቅሰዋል።
ታዳሽ ሀይልን ከማስፋትና የአካባቢ ብክለትን ከመቀነስ አንፃር አስተዋፅኦ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ተጠቃሚነት ለማስፋት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

ጣቢያው በውስጡ 1ሺህ ሰዎችን መያዝ የሚችል ሲኒማቲክ ስክሪን የተገጠመለት አንፊ ቲያትር፣ 2 የህዝብ መዝናኛ ካፍቴሪያዎች እና የህጻናት ማቆያ እንዳሉትም ገልጸዋል።
እንዲሁም 800 ኪሎ ዋት ያለው ዝግጁ ጄኔሬተር ያለው ሲሆን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የተደገፈ የሴኪዩሪቲ ሲስተም እንደተገጠመለትም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026