
አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያላትን ትብብር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ ገለጹ።
ሚኒስትር ዴኤታው ከህንድ የኢንዱስትሪ ማህበር(Confederation of Indian Industry) ባለሀብቶች ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
ውይይቱ ባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሚሰማሩበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
ሚኒስትር ዴኤታው መንግስት የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በዘርፉ ለሚሰማሩ የውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ የኢንዱስትሪ የህግ ማዕቀፍ ከማዘጋጀት ጀምሮ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮች መመቻቸታቸውን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ እና ህንድ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያላቸው ትብብር መጠናከር ለኢንዱስትሪ እድገት እንዲሁም ለቴክኖሎጂና ለዕውቀት ሽግግር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።
ለሀገራቱ ዜጎች የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ከመፍጠር ባሻገር በዓለም አቀፉ ገበያ የጎላ ድርሻ እንዲኖራቸው አስተዋጽኦ ያደርጋል ነው ያሉት።
ከህንድ የኢንዱስትሪ ማህበር የመጡት ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ ምቹ ሁኔታዎች እንዳሉ ለመረዳት እንደቻሉ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026