የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያላትን ትብብር ለማጠናከር ትሻለች - ሚኒስትር ዴኤታ ሀሰን መሐመድ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከህንድ ጋር በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያላትን ትብብር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ ገለጹ።

ሚኒስትር ዴኤታው ከህንድ የኢንዱስትሪ ማህበር(Confederation of Indian Industry) ባለሀብቶች ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

ውይይቱ ባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሚሰማሩበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።

ሚኒስትር ዴኤታው መንግስት የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በዘርፉ ለሚሰማሩ የውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ የኢንዱስትሪ የህግ ማዕቀፍ ከማዘጋጀት ጀምሮ በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮች መመቻቸታቸውን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ እና ህንድ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያላቸው ትብብር መጠናከር ለኢንዱስትሪ እድገት እንዲሁም ለቴክኖሎጂና ለዕውቀት ሽግግር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።

ለሀገራቱ ዜጎች የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ከመፍጠር ባሻገር በዓለም አቀፉ ገበያ የጎላ ድርሻ እንዲኖራቸው አስተዋጽኦ ያደርጋል ነው ያሉት።

ከህንድ የኢንዱስትሪ ማህበር የመጡት ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ ምቹ ሁኔታዎች እንዳሉ ለመረዳት እንደቻሉ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026