የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የባለፉት ዓመታት የድህነት ቅነሳ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ናቸው- የባሌ ዞን ነዋሪዎች</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን ባለፉት ዓመታት ድህነትን ለመቀነስ በተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመልከታቸውን የዞኑ ነዋሪዎች ገለፁ።

በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ውይይት በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ ተካሄዷል።


የውይይቱ ተሳታፊዎች እንዳሉት በዞኑ ባለፉት ዓመታት ግብርናን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ድህነትን ለመቀነስ በተከናወኑ ስራዎች ተስፋ ሰጭ ውጤቶች ተመልክተዋል።

ከተሳታፊዎች መካከል አቶ አህመድ በከር እና አቶ ሐምዛ አደም በተሻሻሉ የግብርና አሰራሮች ምርታማነትን ለማሳደግ የተወሰዱ ዕርምጃዎችን አድንቀዋል።

አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት ይልቅ የውኃ አማራጮችን ተጠቅሞ በስንዴና ገበያ ተኮር ምርቶችን በማልማት ምርትና ምርታማነት እንዲጎለብት መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል።

ወይዘሮ ሐስና ማህሙድ በበኩላቸው የኑሮ ውድነት ዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎችንና የመንግስት ሰራተኛውን እየፈተነ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም መንግስት የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት በልዩ ትኩረት እያከናወነ ያለው ተግባር ማጠናከር እንደሚገባው አንስተዋል።

በተለይም ምርትን በመደበቅ ሰው ሰራሽ የምርት እጥረት የሚፈጥሩ የንግዱ ማህበረሰብ አካላት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ጠቁመዋል።

በአጠቃላይ ሁለንተናዊ የልማት ስራዎችን ማስቀጠል እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት እንዲቀረፉ ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የባሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሐኪም አልይ፤ መንግስት አርሶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በግብርና ግብዓት አቅርቦት ላይ አበክሮ መስራቱን ገልጸዋል።

የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ከፍጆታ እቃዎች ድጎማ ባሻገር አምራችና ሸማቹን በማስተሳሰር ገበያን የማረጋጋት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የዞኑ የልማት ስራዎች ህዝቡን ባሳተፈ አግባብ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አብራርተዋል።

የኦሮሚያ የመስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ፤ ከህዝቡ የተነሱት የመልካም አስተዳደርና የልማት ጥያቄዎች ወሳኝ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ይከናወናሉ ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026