
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።
በሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ የተመራ ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እየተከናወኑ ያሉ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝቷል።
ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፣ በክልሉ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ውጤታማ ናቸው።

በክልሉ በመንግስት እና በግል የኢንቨስትመንት ልማት ስራዎች ላይ የታየው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ጠቁመዋል።
ለኢትዮጵያ ከተሞች የትንሳኤ ዘመን ነው ያሉት ሚኒስትሯ ከተሞቻችን አምራች፣ የፈጠራ ማዕከል እንዲሁም የብልጽግና ማሳያ እንዲሆኑ የተጀመረው ጥረት ውጤታማ ስለመሆኑም አመላክተዋል።
በከተሞች የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድ እና ተዛማጅ የከተማ ልማት ስራ ላይ የተጀመሩ ተግባራትን ቀጣይነት ማረጋገጥ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ምልከታ ባደረጉበት የወልቂጤ ከተማ የሌማት ትሩፋት፣ የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች፣ እያደገ የመጣውን የግብርና ልማት ስራን ወደ ኢንዳስትሪ ማሸጋገር የሚያስችሉ ተቋማትን መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የላቀ አበርክቶ ማድረግ የሚችሉበትን እድል ተፈጥሯል ሲሉም ገልጸዋል።
የግብርና ኢንቨስትመንቱ ለወጣቶች የስራ እድል የሚፈጠርበት፣ የኑሮ ውድነት የሚረጋጋበት፣ ኤክስፖርት አቅምን በማሳደግ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ የሚገኝበት ዘርፍ መሆኑንም ሚኒስትሯ አስረድተዋል።

በወልቂጤ ከተማ የተመሰረተው እልፉ ባልትና ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ የጠንካራ እንስቶች አብነት መሆኑንም ሚኒስትሯ ማስረዳታቸውን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታለ።
በልማት ስራ ጉብኝት መርሐ ግብሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ይሁን አሰፋ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች መገኘታቸውም ተጠቅሷል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026