የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ባለፉት አመታት ተገንብተው ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች መጠናከር አለባቸው</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦በብልጽግና ፓርቲ አመራር ሰጪነት ባለፉት አመታት ተገንብተው ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው የቦንጋ ከተማ ህዝባዊ ኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ገለጹ።

በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት በቦንጋ ከተማ ተካሄዷል።

የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች በፓርቲው መሪነት በተከናወኑ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረው በጉባኤው የተቀመጡ አቅጣጫዎች ተፈፃሚ እንዲሆኑ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ መሰረት ተስፋዬ፣ ባለፉት አመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ እንዳደረጓቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም ተጀምረው የቆዩ የመንገድ፣ የትምህርትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ፈጥነው እንዲጠናቀቁ የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።


ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ አሰገደች ሀይሌ፤ የብልፅግና ፓርቲ ሀገርን ወደ ጥሩ ጎዳና ያሻገረና ህብረተሰቡንም ተጠቃሚ እያደረገ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የቦንጋ ከተማ መጠጥ ውሃ ግንባታ መፋጠን እንዳለበትና በአርብቶ አደር አካባቢ የሚስተዋሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መፍታት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።


በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ፤ ብልፅግና ፓርቲ መሠረታዊ የሆኑ የህዝብ ጥያቄዎችን ለመፍታት እየሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም በርካታ የማንነት፣ የኢኮኖሚና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን እየመለሰ መሆኑን አንስተው አሁንም ከመድረኩ ተሳታፊዎች የተነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በክልልና በፌዴራል መንግስት የሚፈቱበት ሁኔታ እንደሚፈጠርም ተናግረዋል።

ሕዝቡም በየአካባቢው ያለውን እምቅ ሀብት ተጠቅሞ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን ለማሳደግ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ፓርቲው በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤው ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎችና ውሳኔዎች ተፈፃሚ እንዲሆኑ ህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን ተሳትፎና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አቶ አወሉ አሳስበዋል።


ብልፅግና ፓርቲ በበርካታ ጫናዎች ውስጥ አልፎ ድሎችን ማስመዝገቡን የተናገሩት ደግሞ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ጋትሎዋክ ሮን(ዶ/ር) ናቸው።

በእነዚህ ድሎች ውስጥ የህብረተሰቡ ተሳትፎና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ገልፀው በቀጣይም ህዝቡ በየአካባቢው ትብብርና ድጋፉን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከራሱ አልፎ ለሀገር የሚተርፍ ፀጋ ያለው በመሆኑ ይህን ተጠቅሞ ለመበልፀግ አብሮነትና አንድነትን ይጠናከራል ያሉት ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።


ፓርቲው የህዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝና በክልሉ የተጀመሩና ያልተጠናቀቁ የመንገድ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ከፌዴራል መንግስት ጋር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026