የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በሐረሪ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ለሚመልሱ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቷል--አቶ ኦርዲን በድሪ</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ለሚመልሱ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

የሐረሪ ክልል የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።


በተለይ ገቢን በመሰብሰብ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እና በሌማት ትሩፋት ሥራዎች ይበልጥ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለጹት።

የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት፣ ገበያን በማረጋጋትና ህገ ወጥነትን በመከላከል ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አስታውሰዋል።

በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት በኩል ተጨማሪ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል።

ሰው ተኮር በሆኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትም በቀጣይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ተናግረዋል።

በግምገማ መድረኩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና አስፈፃሚ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025