
ሐረር፤ የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ለሚመልሱ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
የሐረሪ ክልል የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።

በተለይ ገቢን በመሰብሰብ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እና በሌማት ትሩፋት ሥራዎች ይበልጥ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለጹት።
የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት፣ ገበያን በማረጋጋትና ህገ ወጥነትን በመከላከል ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አስታውሰዋል።
በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት በኩል ተጨማሪ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል።
ሰው ተኮር በሆኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትም በቀጣይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ተናግረዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና አስፈፃሚ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026