
ሐረር፤ የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ለሚመልሱ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
የሐረሪ ክልል የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።

በተለይ ገቢን በመሰብሰብ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እና በሌማት ትሩፋት ሥራዎች ይበልጥ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለጹት።
የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት፣ ገበያን በማረጋጋትና ህገ ወጥነትን በመከላከል ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አስታውሰዋል።
በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት በኩል ተጨማሪ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል።
ሰው ተኮር በሆኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትም በቀጣይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ተናግረዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና አስፈፃሚ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026