
ሐረር፤ የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ለሚመልሱ ሥራዎች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
የሐረሪ ክልል የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።

በተለይ ገቢን በመሰብሰብ፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እና በሌማት ትሩፋት ሥራዎች ይበልጥ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለጹት።
የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስፋት፣ ገበያን በማረጋጋትና ህገ ወጥነትን በመከላከል ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም አስታውሰዋል።
በኢንዱስትሪና በማኑፋክቸሪንግ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት በኩል ተጨማሪ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል።
ሰው ተኮር በሆኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትም በቀጣይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ተናግረዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና አስፈፃሚ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026