የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ኮሪደር ልማት የባሕር ዳር ከተማን እና የጣና ሐይቅን ውበት አጉልቷል</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ የካቲት 18/2017( ኢዜአ)፦ የኮሪደር ልማት የጣና ሐይቅን ውበት የገለጠ እና የባሕር ዳርን ቱሪስት መዳረሻነት የሚያጎላ ነው ሲሉ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ገለፁ።

ሚኒስትሯና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ኮሪደር ልማትን ጨምሮ የባሕር ዳር ከተማ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

ሚኒስትሯ እንዳሉት የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎች የጣናን ውበት የገለጡና ባሕር ዳርን የቱሪስት መዳረሻነት የሚያጎሉ ናቸው።

የኮሪደር ልማት የከተማዋ ነዋሪዎች የኑሮ ዘይቤ የሚያሻሽል እንደሆነም ገልፀዋል።

የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዮም ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃ በማሟላት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ እየተገነባ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ለከተማዋ ተጨማሪ ፀጋ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፤ በከተማዋ ሁለንተናዊ ጠቀሜታ ያላቸው የኮሪደር ልማትና ሌሎችም የልማት ፕሮጀክቶች እየተፋጠኑ መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ የከተማዋን ውበት የሚገልጡ እና የዜጎችን ተጠቃሚነት እንደሚያሳድጉ ገልጸዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተሞችና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ የከተሞችን ገፅታ የሚቀይሩ የኮሪደር የልማት ስራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።


ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻና ደብረ ብርሃን ከተሞች ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ኮሪደር እየተሸጋገሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ኮሪደር ልማት ከተሞችን ውብ፣ ተወዳዳሪና የቱሪስት መዳረሻ የሚያደርግና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸውም ብለዋል።

የባሕር ዳር ኮሪደር ልማት በተያዘለት ጊዜ ገደብ አግባብ እየተከናወነ መሆኑን ደግሞ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ተናግረዋል።


ስራው ከጣና ሐይቅ ጋር ተሳስሮ በጥራት እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ እየተጠናቀቀ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026