የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የስራ ምልከታ አድርገዋል፡፡

የሱፐርቪዥን ቡድኑ በተቋሙ የበለፀጉ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የቴክኖሎጂ ስራዎችን መገምገሙንና በኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውሮ መመልከቱን ከኢንስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡


የኢንስቲትዩቱን ስራዎች በተመለከተ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ዝርዝር ማብራሪያ ማቅረባቸውም ተገልጿል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ከዕድሜው በላይ የሆኑ ስራዎች መስራቱን የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ ዶክተር ቀነዓ ያደታ አንስተው ተቋሙ ለሀገር ትልቅ አቅም እንደሆነ መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡


ይህን አቅም በተለያዩ ዘርፎች ለሚታዩ ችግሮች መፍቻ ቁልፍ ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅርበት መስራት እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡

በኢንስቲትዩቱ በበለፀጉ የቴክኖሎጂ ስራዎች የብዙኃንን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንጻር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር ኢንስቲትዩቱ በቅንጅት ስለሚሰራበት አግባብ በሱፐርቪዥን ቡድኑ አባላት ጥያቄዎች ቀርበው በዋና ዳይሬክተሩ ምላሽ እንደተሰጣቸውም ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025