
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የስራ ምልከታ አድርገዋል፡፡
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በተቋሙ የበለፀጉ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የቴክኖሎጂ ስራዎችን መገምገሙንና በኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውሮ መመልከቱን ከኢንስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢንስቲትዩቱን ስራዎች በተመለከተ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ዝርዝር ማብራሪያ ማቅረባቸውም ተገልጿል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ከዕድሜው በላይ የሆኑ ስራዎች መስራቱን የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ ዶክተር ቀነዓ ያደታ አንስተው ተቋሙ ለሀገር ትልቅ አቅም እንደሆነ መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡

ይህን አቅም በተለያዩ ዘርፎች ለሚታዩ ችግሮች መፍቻ ቁልፍ ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅርበት መስራት እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በኢንስቲትዩቱ በበለፀጉ የቴክኖሎጂ ስራዎች የብዙኃንን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንጻር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር ኢንስቲትዩቱ በቅንጅት ስለሚሰራበት አግባብ በሱፐርቪዥን ቡድኑ አባላት ጥያቄዎች ቀርበው በዋና ዳይሬክተሩ ምላሽ እንደተሰጣቸውም ተገልጿል፡፡
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026