የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ማዕከሉ በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS


ቦንጋ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።


በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል ከተቋቋመ ስምንት ወራት አስቆጥሯል።


ማእከሉ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁንም ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በብዛትና በጥራት በማቅረብ ላይ ይገኛል።


የማእከሉን የስራ እንቅስቃሴ በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማዕከሉ ኃላፊ አቶ ያሲን አባጊሶ፤ የማዕከሉ አገልግሎት በተለይም ለቡና ነጋዴዎችና ኤክስፖርተሮች የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት ብቻ 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን ገልጸዋል።


ከካፋ ዞን በተጨማሪ ከሸካና ቤንች ሸኮ አካባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፥ ቡናው ተመርምሮ ደረጃ ከወጣለት በኋላ በቀጥታ ውል መሠረት ግብይት እንደሚፈፀምም ተናግረዋል።


የነጋዴዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ሰይድ ሳኒሀሰን፤ የቦንጋ ማዕከል ከተከፈተ በኋላ የነበረው እንግልትና ያልተገባ ወጪ መቅረቱን አንስተዋል።


ሌላው የቡና አቅራቢዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ወንድዬ ምትኩ፤ ከዚህ ቀደም በጅማ ማዕከል ላይ በነበረው ጫና መኪኖች ቡና ጭነው ለበርካታ ቀናት ስለሚቆዩ ከፍተኛ ችግር እንደነበር አስታውሰው፥ የማእከሉ መከፈት እነዚህን ሁሉ ችግሮች አስቀርቷል ብለዋል።


የቦንጋ ማዕከል ስራ በመጀመሩ የቡና ምርት በአጭር ጊዜ ውስጥ ደረጃ ወጥቶለት ለገበያ ማቅረብ አስችሏል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026