ቦንጋ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል ከተቋቋመ ስምንት ወራት አስቆጥሯል።
ማእከሉ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁንም ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በብዛትና በጥራት በማቅረብ ላይ ይገኛል።
የማእከሉን የስራ እንቅስቃሴ በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማዕከሉ ኃላፊ አቶ ያሲን አባጊሶ፤ የማዕከሉ አገልግሎት በተለይም ለቡና ነጋዴዎችና ኤክስፖርተሮች የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት ብቻ 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን ገልጸዋል።
ከካፋ ዞን በተጨማሪ ከሸካና ቤንች ሸኮ አካባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፥ ቡናው ተመርምሮ ደረጃ ከወጣለት በኋላ በቀጥታ ውል መሠረት ግብይት እንደሚፈፀምም ተናግረዋል።
የነጋዴዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ሰይድ ሳኒሀሰን፤ የቦንጋ ማዕከል ከተከፈተ በኋላ የነበረው እንግልትና ያልተገባ ወጪ መቅረቱን አንስተዋል።
ሌላው የቡና አቅራቢዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ወንድዬ ምትኩ፤ ከዚህ ቀደም በጅማ ማዕከል ላይ በነበረው ጫና መኪኖች ቡና ጭነው ለበርካታ ቀናት ስለሚቆዩ ከፍተኛ ችግር እንደነበር አስታውሰው፥ የማእከሉ መከፈት እነዚህን ሁሉ ችግሮች አስቀርቷል ብለዋል።
የቦንጋ ማዕከል ስራ በመጀመሩ የቡና ምርት በአጭር ጊዜ ውስጥ ደረጃ ወጥቶለት ለገበያ ማቅረብ አስችሏል ተብሏል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025