የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ማዕከሉ በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS


ቦንጋ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።


በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል ከተቋቋመ ስምንት ወራት አስቆጥሯል።


ማእከሉ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁንም ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በብዛትና በጥራት በማቅረብ ላይ ይገኛል።


የማእከሉን የስራ እንቅስቃሴ በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማዕከሉ ኃላፊ አቶ ያሲን አባጊሶ፤ የማዕከሉ አገልግሎት በተለይም ለቡና ነጋዴዎችና ኤክስፖርተሮች የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት ብቻ 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን ገልጸዋል።


ከካፋ ዞን በተጨማሪ ከሸካና ቤንች ሸኮ አካባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፥ ቡናው ተመርምሮ ደረጃ ከወጣለት በኋላ በቀጥታ ውል መሠረት ግብይት እንደሚፈፀምም ተናግረዋል።


የነጋዴዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ሰይድ ሳኒሀሰን፤ የቦንጋ ማዕከል ከተከፈተ በኋላ የነበረው እንግልትና ያልተገባ ወጪ መቅረቱን አንስተዋል።


ሌላው የቡና አቅራቢዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ወንድዬ ምትኩ፤ ከዚህ ቀደም በጅማ ማዕከል ላይ በነበረው ጫና መኪኖች ቡና ጭነው ለበርካታ ቀናት ስለሚቆዩ ከፍተኛ ችግር እንደነበር አስታውሰው፥ የማእከሉ መከፈት እነዚህን ሁሉ ችግሮች አስቀርቷል ብለዋል።


የቦንጋ ማዕከል ስራ በመጀመሩ የቡና ምርት በአጭር ጊዜ ውስጥ ደረጃ ወጥቶለት ለገበያ ማቅረብ አስችሏል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025