የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ማዕከሉ በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS


ቦንጋ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።


በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል ከተቋቋመ ስምንት ወራት አስቆጥሯል።


ማእከሉ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁንም ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በብዛትና በጥራት በማቅረብ ላይ ይገኛል።


የማእከሉን የስራ እንቅስቃሴ በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማዕከሉ ኃላፊ አቶ ያሲን አባጊሶ፤ የማዕከሉ አገልግሎት በተለይም ለቡና ነጋዴዎችና ኤክስፖርተሮች የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም የቦንጋ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርተፍኬሽን ማዕከል በስምንት ወራት ብቻ 53 ሺህ 14 ቶን ደረቅና የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን ገልጸዋል።


ከካፋ ዞን በተጨማሪ ከሸካና ቤንች ሸኮ አካባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፥ ቡናው ተመርምሮ ደረጃ ከወጣለት በኋላ በቀጥታ ውል መሠረት ግብይት እንደሚፈፀምም ተናግረዋል።


የነጋዴዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ሰይድ ሳኒሀሰን፤ የቦንጋ ማዕከል ከተከፈተ በኋላ የነበረው እንግልትና ያልተገባ ወጪ መቅረቱን አንስተዋል።


ሌላው የቡና አቅራቢዎች እና ኤክስፖርተሮች ወኪል አቶ ወንድዬ ምትኩ፤ ከዚህ ቀደም በጅማ ማዕከል ላይ በነበረው ጫና መኪኖች ቡና ጭነው ለበርካታ ቀናት ስለሚቆዩ ከፍተኛ ችግር እንደነበር አስታውሰው፥ የማእከሉ መከፈት እነዚህን ሁሉ ችግሮች አስቀርቷል ብለዋል።


የቦንጋ ማዕከል ስራ በመጀመሩ የቡና ምርት በአጭር ጊዜ ውስጥ ደረጃ ወጥቶለት ለገበያ ማቅረብ አስችሏል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026