የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የጃፓኑ ኩባንያ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የሶላር ፓናል ማምረት ጀመረ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡-በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በ60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተለያዩ ሶላር ፓኔሎችን ለማምረት የገባው የጃፓኑ ቶዮ ሶላር ኩባንያ የማሽን ተከላ ስራዎችን በማጠናቀቅ የሙከራ ምርት ማምረት ጀምሯል።


የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር)፥ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ የቶዮ ሶላር ኩባንያን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል፡፡


ዋና ስራ አስፈጻሚው፥ ኩባንያው በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሂደት እንዲገባ ኮርፖሬሸኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።


የኩባንያው የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው የግንባታ ስራውን ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ መጋቢት አጋማሽ ላይ በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሂደት እንደሚገባ ጠቁመዋል።


ኩባንያው በተያዘው በጀት ዓመት በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ስራ ለመጀመር ከኮርፖሬሽኑ ጋር ተፈራርሞ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ምርቶቹንም ወደ መካከለኛው ምስራቅ ፤ ህንድ እና አሜሪካ እንደሚልክ አስታውቋል፡፡


ቶዮ ሶላር ኩባንያ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ሶስት ሄክታር የለማ መሬት እና የማምረቻ ሼድ ተረክቦ ስራ ጀምሯል።


ኩባንያው ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ቬትናም ውስጥ የሶላር ፓናል ማምረቻ ፋብሪካ አለው።


ኩባንያው በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሂደት ሲጋበ ከአንድ ሺህ በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ቋሚ የስራ እድልን እንደሚፈጥር የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026