
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡-በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በ60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተለያዩ ሶላር ፓኔሎችን ለማምረት የገባው የጃፓኑ ቶዮ ሶላር ኩባንያ የማሽን ተከላ ስራዎችን በማጠናቀቅ የሙከራ ምርት ማምረት ጀምሯል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር)፥ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ የቶዮ ሶላር ኩባንያን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው፥ ኩባንያው በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሂደት እንዲገባ ኮርፖሬሸኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የኩባንያው የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው የግንባታ ስራውን ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ መጋቢት አጋማሽ ላይ በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሂደት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ኩባንያው በተያዘው በጀት ዓመት በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ስራ ለመጀመር ከኮርፖሬሽኑ ጋር ተፈራርሞ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ምርቶቹንም ወደ መካከለኛው ምስራቅ ፤ ህንድ እና አሜሪካ እንደሚልክ አስታውቋል፡፡
ቶዮ ሶላር ኩባንያ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ሶስት ሄክታር የለማ መሬት እና የማምረቻ ሼድ ተረክቦ ስራ ጀምሯል።
ኩባንያው ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ቬትናም ውስጥ የሶላር ፓናል ማምረቻ ፋብሪካ አለው።
ኩባንያው በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሂደት ሲጋበ ከአንድ ሺህ በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ቋሚ የስራ እድልን እንደሚፈጥር የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026