
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ተጀምሯል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፋይዳ ምዝገባ አፈፃፀም ግምገማና የተማሪዎች የምዝገባ ማስጀመርያ መርሃ ግብር ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ዋና ስራ-አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፣ የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዮዳሄ አርዓያስላሴ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት፤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል፡፡
በዚህ ወቅትም የተማሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ጋር በትብብር እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026