
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ተጀምሯል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፋይዳ ምዝገባ አፈፃፀም ግምገማና የተማሪዎች የምዝገባ ማስጀመርያ መርሃ ግብር ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ዋና ስራ-አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፣ የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዮዳሄ አርዓያስላሴ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት፤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል፡፡
በዚህ ወቅትም የተማሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ጋር በትብብር እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026