
ባህርዳር፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ግብርን በወቅቱ በመክፈል በአገራችን ልማት ላይ አሻራችንን የማሳረፉን ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአማራ ክልል ምስጉን ግብር ከፋዮች ገለጹ።
በባህር ዳር የሚገኘው የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል አባተ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የምንከፍለው ግብር ለጤና፣ ለትምህርት፣ለመንገድና ለተለያዩ የልማት ስራዎች እየዋለ መሆኑን ተገንዝበናል።
ግብር መክፈል ክብር፣ግብርን መሰወር ግን የሃገርን እድገት እንደሚጎዳ በመረዳት ከስወራ መታቀብ እንደሚገባም አቶ ዳንኤል መክረዋል።
ይህን በመረዳትም ሪዞርታቸው በ2016 በጀት ዓመት ካገኘው ገቢ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ግብር በመክፈል እውቅናና ሽልማት ማግኘቱን አስረድተዋል።
ግብራቸውን በፍትሃዊነት ለሚከፍሉ ድርጅቶችና ባለሃብቶች እንደዚህ አይነት እውቅና መሰጠቱ በህገወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙትን ወደ ህጋዊነት ለመመለስ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።
የአዲናስ ጠቅላላ ሆስፒታል የፋይናንስ ኃላፊ አቶ አማረ አያሌው በበኩላቸው፥ ለእውቅናና ሽልማት የበቁት ግብር የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብም ከድርጅቱና ከሰራተኞች የሚሰበሰበውን በፍላጎትና በራስ ተነሳሽነት መክፈል በመቻላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
የእውቅና ሽልማት መሰጠቱ አበረታች ተግባር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመው፥ የግብር አከፋፈል ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በገቢዎች ሚኒስቴር ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ደመመ እንደገለጹት ባለፉት ሰባት ወራት በቅርንጫፉ ከ5 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ለሃገር ልማት አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።
ለዚህ ግብር መሰብሰብ ግንባር ቀደም የሆኑና የህግ ተገዥነትን በማክበር ሀገራዊ ግዴታቸውን ለተወጡ ምስጉን ግብር ከፋዮች እውቅና መስጠት ጀግናን ከማክበር የተለየ አይደለም ብለዋል።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮና ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሰሞኑን ያካሄደውን የምስጉን ግብር ከፋዮች የእውቅናና የሽልማት ስነ ስርዓት መካሄዱ ይታወሳል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026