የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ግብርን በወቅቱ በመክፈል በአገራችን ልማት ላይ አሻራችንን የማሳረፉን ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ግብርን በወቅቱ በመክፈል በአገራችን ልማት ላይ አሻራችንን የማሳረፉን ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአማራ ክልል ምስጉን ግብር ከፋዮች ገለጹ።


በባህር ዳር የሚገኘው የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል አባተ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የምንከፍለው ግብር ለጤና፣ ለትምህርት፣ለመንገድና ለተለያዩ የልማት ስራዎች እየዋለ መሆኑን ተገንዝበናል።


ግብር መክፈል ክብር፣ግብርን መሰወር ግን የሃገርን እድገት እንደሚጎዳ በመረዳት ከስወራ መታቀብ እንደሚገባም አቶ ዳንኤል መክረዋል።


ይህን በመረዳትም ሪዞርታቸው በ2016 በጀት ዓመት ካገኘው ገቢ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ግብር በመክፈል እውቅናና ሽልማት ማግኘቱን አስረድተዋል።


ግብራቸውን በፍትሃዊነት ለሚከፍሉ ድርጅቶችና ባለሃብቶች እንደዚህ አይነት እውቅና መሰጠቱ በህገወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙትን ወደ ህጋዊነት ለመመለስ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።


የአዲናስ ጠቅላላ ሆስፒታል የፋይናንስ ኃላፊ አቶ አማረ አያሌው በበኩላቸው፥ ለእውቅናና ሽልማት የበቁት ግብር የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብም ከድርጅቱና ከሰራተኞች የሚሰበሰበውን በፍላጎትና በራስ ተነሳሽነት መክፈል በመቻላቸው መሆኑን አስረድተዋል።


የእውቅና ሽልማት መሰጠቱ አበረታች ተግባር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመው፥ የግብር አከፋፈል ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


በገቢዎች ሚኒስቴር ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ደመመ እንደገለጹት ባለፉት ሰባት ወራት በቅርንጫፉ ከ5 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ለሃገር ልማት አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።


ለዚህ ግብር መሰብሰብ ግንባር ቀደም የሆኑና የህግ ተገዥነትን በማክበር ሀገራዊ ግዴታቸውን ለተወጡ ምስጉን ግብር ከፋዮች እውቅና መስጠት ጀግናን ከማክበር የተለየ አይደለም ብለዋል።


የክልሉ ገቢዎች ቢሮና ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሰሞኑን ያካሄደውን የምስጉን ግብር ከፋዮች የእውቅናና የሽልማት ስነ ስርዓት መካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026