የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>ግብርን በወቅቱ በመክፈል በአገራችን ልማት ላይ አሻራችንን የማሳረፉን ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ግብርን በወቅቱ በመክፈል በአገራችን ልማት ላይ አሻራችንን የማሳረፉን ተግባር አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአማራ ክልል ምስጉን ግብር ከፋዮች ገለጹ።


በባህር ዳር የሚገኘው የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል አባተ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የምንከፍለው ግብር ለጤና፣ ለትምህርት፣ለመንገድና ለተለያዩ የልማት ስራዎች እየዋለ መሆኑን ተገንዝበናል።


ግብር መክፈል ክብር፣ግብርን መሰወር ግን የሃገርን እድገት እንደሚጎዳ በመረዳት ከስወራ መታቀብ እንደሚገባም አቶ ዳንኤል መክረዋል።


ይህን በመረዳትም ሪዞርታቸው በ2016 በጀት ዓመት ካገኘው ገቢ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ግብር በመክፈል እውቅናና ሽልማት ማግኘቱን አስረድተዋል።


ግብራቸውን በፍትሃዊነት ለሚከፍሉ ድርጅቶችና ባለሃብቶች እንደዚህ አይነት እውቅና መሰጠቱ በህገወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙትን ወደ ህጋዊነት ለመመለስ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።


የአዲናስ ጠቅላላ ሆስፒታል የፋይናንስ ኃላፊ አቶ አማረ አያሌው በበኩላቸው፥ ለእውቅናና ሽልማት የበቁት ግብር የዜግነት ግዴታ መሆኑን በመገንዘብም ከድርጅቱና ከሰራተኞች የሚሰበሰበውን በፍላጎትና በራስ ተነሳሽነት መክፈል በመቻላቸው መሆኑን አስረድተዋል።


የእውቅና ሽልማት መሰጠቱ አበረታች ተግባር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመው፥ የግብር አከፋፈል ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


በገቢዎች ሚኒስቴር ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ደመመ እንደገለጹት ባለፉት ሰባት ወራት በቅርንጫፉ ከ5 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ለሃገር ልማት አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።


ለዚህ ግብር መሰብሰብ ግንባር ቀደም የሆኑና የህግ ተገዥነትን በማክበር ሀገራዊ ግዴታቸውን ለተወጡ ምስጉን ግብር ከፋዮች እውቅና መስጠት ጀግናን ከማክበር የተለየ አይደለም ብለዋል።


የክልሉ ገቢዎች ቢሮና ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሰሞኑን ያካሄደውን የምስጉን ግብር ከፋዮች የእውቅናና የሽልማት ስነ ስርዓት መካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026