
ይርጋለም፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):- ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤክስፖርትና ተኪ ምርቶችን በማምረት በአገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡
በፓርኩ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ አራት ባለሀብቶችን ስራ የማስጀመርና የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን የማስመረቅ መርሃግብር ዛሬ ተከናውኗል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሐሰን መሀመድ እንዳሉት የተቀናጁ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርኮች እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ፣ ወጪ ምርትን በማሳደግና ከውጭ የሚገቡትን በመተካት ሚናቸው ጉልህ ነው፡፡
ፓርኮቹ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን መዋቅራዊ ሽግግር በማጠናከር ለአገር ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል፡፡
ከእነዚህ አንዱ የሆነው ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ኢንዱስትሪ ፓርክ የወጪና ተኪ ምርቶችን በማምረት በአገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የይርጋለም የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቦርድ ሰብሳቢና የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) በበኩላቸው በፓርኩ ስራ የጀመሩ ፋብሪካዎች ተገቢውን ግብዓት እንዲያገኙ ምርታማነትን የማሳደጉ ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በፓርኩ የዛሬዎቹን ጨምሮ ስምንት ባለሃብቶች በአቡካዶ ዘይት፣ በወተት፣ በማርና ቡና ምርት የማቀነባበር ስራ እያከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሃይሉ የተራ ናቸው፡፡
ዛሬ ወደ ስራ የገቡት አራት ባለሃብቶች ከአንድ ቢለዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው አንድ ሺህ ለሚጠጉ ዜጎችም ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ፓርኩ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ23ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረና ምርታማነቱ እያደገ በመሆኑ የግብዓት፣የመሰረተ ልማትና የግብይት ስርዓቱን ለማሳለጥ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
አዳዲስ ፋብሪካዎቹን ስራ ከማስጀመር በተጨማሪ በቀን 200 ሜትሪ ኪዩብ ፈሳሽ ቆሻሻ የሚያጣራ ፕላንት፣ የአንድ መስኮት አገልግሎት ማእከልና የህጻናት ማቆያም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026