የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የኢንዱስትሪ ፓርኩ የወጪና ተኪ ምርቶችን በማምረት በአገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው - ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ይርጋለም፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):- ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤክስፖርትና ተኪ ምርቶችን በማምረት በአገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

በፓርኩ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ አራት ባለሀብቶችን ስራ የማስጀመርና የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን የማስመረቅ መርሃግብር ዛሬ ተከናውኗል፡፡


በመርሃ ግብሩ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሐሰን መሀመድ እንዳሉት የተቀናጁ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርኮች እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ፣ ወጪ ምርትን በማሳደግና ከውጭ የሚገቡትን በመተካት ሚናቸው ጉልህ ነው፡፡

ፓርኮቹ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን መዋቅራዊ ሽግግር በማጠናከር ለአገር ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል፡፡

ከእነዚህ አንዱ የሆነው ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ኢንዱስትሪ ፓርክ የወጪና ተኪ ምርቶችን በማምረት በአገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የይርጋለም የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቦርድ ሰብሳቢና የሲዳማ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አራርሶ ገረመው(ዶ/ር) በበኩላቸው በፓርኩ ስራ የጀመሩ ፋብሪካዎች ተገቢውን ግብዓት እንዲያገኙ ምርታማነትን የማሳደጉ ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በፓርኩ የዛሬዎቹን ጨምሮ ስምንት ባለሃብቶች በአቡካዶ ዘይት፣ በወተት፣ በማርና ቡና ምርት የማቀነባበር ስራ እያከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሃይሉ የተራ ናቸው፡፡

ዛሬ ወደ ስራ የገቡት አራት ባለሃብቶች ከአንድ ቢለዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰው አንድ ሺህ ለሚጠጉ ዜጎችም ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡

ፓርኩ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ23ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረና ምርታማነቱ እያደገ በመሆኑ የግብዓት፣የመሰረተ ልማትና የግብይት ስርዓቱን ለማሳለጥ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡

አዳዲስ ፋብሪካዎቹን ስራ ከማስጀመር በተጨማሪ በቀን 200 ሜትሪ ኪዩብ ፈሳሽ ቆሻሻ የሚያጣራ ፕላንት፣ የአንድ መስኮት አገልግሎት ማእከልና የህጻናት ማቆያም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026