
ጭሮ ፤የካቲት 22/2017 (ኢዜአ)፡-የጭሮ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ የተመረቁበትን ሙያ ወደ ተግባር ለመለወጥ ዕድል እንደፈጠረላቸው የከተማው ወጣቶች ገለጹ፡፡
በማህበር ተደራጅተው በኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ያገኙ የከተማው ወጣቶች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተመረቁበት ሙያ በኮሪደር ልማቱ ስራ በመሰማራት ገቢ ከማግኘታቸውም በላይ ሙያቸውን ወደ ተግባር ለመለወጥ እድል አግኝተዋል፡፡
በኮሪደር ልማቱ ስራ ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ጀማል ኑሬ አህመድ፤ ከጅማ ዩኒቨርስቲ በስቪል ምህንድስና በመጀመርያ ዲግሪ ተመርቋል፡፡
ወጣቱ እንደሚለው በከተማ ማዘመን፣ በመንገድ መሰረተ ልማትና መሰል ሙያዎች የቀሰመውን ትምህርት ወደ ተግባር ለመለወጥ የኮሪደር ልማቱ እድል ፈጥሮለታል፡፡
መንግስት በኮሪደር ልማት የተሻለ ከተማ ለመፍጠር እየሰራ ያለው ስራ ከተሞችን ለኑሮ ምቹ ለማድረግና ቱሪዝምን ለማነቃቃት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግሯል፡፡
በዩኒቨርስቲ የቀሰመውን ሙያ ወደ ተግባር በመለወጥ በኮሪደር ልማቱ የበኩሉን አስተዋጽዎ እያበረከተ መሆኑን ገልጿል።
ከጨርጨር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግንባታ ሙያ የተመረቀው ወጣት ሻፊ መሀመድ በበኩሉ የኮሪደር ልማቱ ከስራ ዕድል ፈጠራ በተጨማሪ ሙያውን ለማሳደግ ዕድል ፈጥሮለታል፡፡
''በኮሪደር ልማቱ በንቃት በመሳተፍ አሻራዬን ለማኖር እሰራሁ ነው'' ያለው ወጣቱ በቀጣይ በትላልቅ የግንባታ መስኮች ለመሰማራት ራዕይ እንዳለው ተናግሯል፡፡
በኮሪደር ልማቱ የተከናወኑ የመንገድ ዳር ማስዋብ፤ የአረንጓዴ ልማት እና መሰል ስራዎች በትምህርት የቀሰመውን ሙያ በተግባር ለማዳበር ትልቅ አስተዋጽዎ እያበረከተለት መሆኑን የተናገረው ደግሞ ሌላኛው ከፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሰርቬይንግ ትምህርት መስክ በዲፕሎማ የተመረቀው ወጣት የሱፍ ቀመር ነው፡፡
''በኮሪደር ልማቱ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከሙያዬ ጋር ተያያዥ ናቸው'' ያለው ወጣቱ ይህም ሙያውን እንዲያሳድግ አስተዋጽዎ እንደፈጠርለት ተናግሯል፡፡
''የኮሪደር ልማት ከፈጠረልኝ የስራ ዕድል ባለፈ ተጨማሪ ሙያዎችን እንድለምድ እያገዘኝ ነው'' ብሏል ወጣቱ፡፡

የጭሮ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዝና ስራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት የስራ ዕድል ፈጠራና ክትትል ቡድን መሪ አቶ ወርቅነህ ተስፋዬ እንደገለጹት በበጀት አመቱ 437 ወጣቶች የኮሪደር ልማትና ተያያዥ በሆነ የግንባታ መስክ በ23 ማህበራት ተደራጅተው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡
በማህበራት ከተደራጁት ወጣቶች መካከል የተወሰኑት ወጣቶች ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው በኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡
ወጣቶቹ በስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ስልጠናዎች እና ሌሎች ድጋፎች እንደተደረገላቸው አመልክተዋል፡፡
የጭሮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጀማል ጎሳዬ በበኩላቸው በከተማው የመንገድ ዳር ውበትና፣ አነስተኛ ድልድዮችና አደባባይ ግንባታን ያካተተ የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
በኮሪደር ልማቱ ነዋሪዎች የመንገድ ዳር ትርፍ ይዞታዎችን በማንሳት እንዲሁም ባለሀብቶች በንግድ ቤቶቻቸው ፊትለፊት የሚከናውን የእግረኛ መንገድ ለማስዋብ ቃል መግባታቸውን አመልክተዋል፡፡
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026