
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ የሸገር ከተማን በታቀደው መሰረት ዘመናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለማልማት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የፋይናንስ ተቋማትና የሸገር ከተማ አስተዳደር ቅንጅታዊ አሰራርን ለማጠናከር ያለመ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።
ከንቲባው በመድረኩ ላይ ሸገር ከተማ በሀሳብና በአደረጃጀት ዘመኑን በሚመጥን መልኩ የሚመራ ከተማ ነው ብለዋል።

ከተማው ከተመሰረተ ጀምሮ አስፈላጊ ዝግጅቶች ሲያደርግ ቆይቶ አሁን ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለይ በመሬት አጠቃቀም፣ የከተማ አስተዳደሩ የሚመራባቸው ህጎችና ስርዓቶች እንዲሁም ለአንድ ዘመናዊ ከተማ የሚያስፈልጉ ሂደቶች አየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ሂደት የባለሀብቶችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው አስተዳደሩ ወሳኝ ከሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም የኢንቨስትመንት እድሎችን ጨምሮ በከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተዋል።
በዛሬው መድረክም ከተማውን በተሻለ መልኩ ለመምራትና ለማስተዳደር ከትልልቅ ፋይናንስ ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን አስረድተዋል።
በቀጣይም ከተማ አስተዳደሩ የተሻለች ከተማን እውን ለማድረግ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026