የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የሸገር ከተማ ዘመናዊነትን ጠብቆ ለማልማት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ የሸገር ከተማን በታቀደው መሰረት ዘመናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለማልማት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ተናገሩ።

የፋይናንስ ተቋማትና የሸገር ከተማ አስተዳደር ቅንጅታዊ አሰራርን ለማጠናከር ያለመ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።

ከንቲባው በመድረኩ ላይ ሸገር ከተማ በሀሳብና በአደረጃጀት ዘመኑን በሚመጥን መልኩ የሚመራ ከተማ ነው ብለዋል።


ከተማው ከተመሰረተ ጀምሮ አስፈላጊ ዝግጅቶች ሲያደርግ ቆይቶ አሁን ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተለይ በመሬት አጠቃቀም፣ የከተማ አስተዳደሩ የሚመራባቸው ህጎችና ስርዓቶች እንዲሁም ለአንድ ዘመናዊ ከተማ የሚያስፈልጉ ሂደቶች አየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ሂደት የባለሀብቶችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው አስተዳደሩ ወሳኝ ከሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል።

በዚህም የኢንቨስትመንት እድሎችን ጨምሮ በከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተዋል።

በዛሬው መድረክም ከተማውን በተሻለ መልኩ ለመምራትና ለማስተዳደር ከትልልቅ ፋይናንስ ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን አስረድተዋል።

በቀጣይም ከተማ አስተዳደሩ የተሻለች ከተማን እውን ለማድረግ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026