
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ የሸገር ከተማን በታቀደው መሰረት ዘመናዊነትን በጠበቀ መልኩ ለማልማት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የፋይናንስ ተቋማትና የሸገር ከተማ አስተዳደር ቅንጅታዊ አሰራርን ለማጠናከር ያለመ የውይይት መድረክ ተካሄዷል።
ከንቲባው በመድረኩ ላይ ሸገር ከተማ በሀሳብና በአደረጃጀት ዘመኑን በሚመጥን መልኩ የሚመራ ከተማ ነው ብለዋል።

ከተማው ከተመሰረተ ጀምሮ አስፈላጊ ዝግጅቶች ሲያደርግ ቆይቶ አሁን ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለይ በመሬት አጠቃቀም፣ የከተማ አስተዳደሩ የሚመራባቸው ህጎችና ስርዓቶች እንዲሁም ለአንድ ዘመናዊ ከተማ የሚያስፈልጉ ሂደቶች አየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ሂደት የባለሀብቶችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው አስተዳደሩ ወሳኝ ከሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያደረገ መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም የኢንቨስትመንት እድሎችን ጨምሮ በከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተዋል።
በዛሬው መድረክም ከተማውን በተሻለ መልኩ ለመምራትና ለማስተዳደር ከትልልቅ ፋይናንስ ተቋማት ጋር ውይይት መደረጉን አስረድተዋል።
በቀጣይም ከተማ አስተዳደሩ የተሻለች ከተማን እውን ለማድረግ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026