
ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ)፦ የይርጋለም አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ እሴት የተጨመረባቸውን የግብርና ምርቶች በማምረት በዘርፉ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በፓርክ የተሰማሩ ኩባንያዎች ገለጹ።
ምቹ መሰረተ ልማት ያሟላው ፓርኩ፤ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን በመትከል ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግና የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንዳስቻለም ተናግረዋል።
ኢዜአ ካነጋገራቸው ባለሀብቶች መካከል የጎልደን ኦርጋኒክ ኦይልና የፋሚሊ ሃኒ ፋብሪካ ባለቤት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል በፓርኩ አቮካዶና ማር የሚያቀነባብሩ ሁለት ፋብሪካዎቻቸውን ወደሥራ አስገብተዋል።
ባለሀብቱ እንዳሉት ከአቮካዶ ዘይት ፋብሪካው ብቻ በዓመት እስከ 1 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ያቀዱ ሲሆን እሴት የተጨመረበት የማር ምርት ለማቀነባበርም እየሰሩ ነው።
ለፋብሪካዎቹ ግብዓት የሚያቀርበውን የእርሻ ፕሮጀክት ጨምሮ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ወደ ማቀነባበር ሥራ መግባታቸውንም ኢንጂነር ዘላለም አስረድተዋል።
ከአቮካዶና የማር ምርት ከሚያቀርቡ ከ110 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ጋር የገበያ ትስስር መፈጠሩን ገልጸው፣ በዚህም ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡

የሔብሮን ኮፊ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሮምዮ ዛራሜላ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ ዕሴት የተጨረበት ቡና ወደ ውጭ ለመላክ እየተንቀሰቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።
ፋብሪካው በቀን እስከ 2 ሺህ ኪሎ ግራም ቡና የመቁላት ዕቅድ እንዳለው ጠቅሰው፤ ከ10 ሺህ አርሶ አደሮች ጋር ትስስር በመፍጠር ለአርሶ አደሮችም ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ስለመሆኑ አንስተዋል።
የ'ኢትዮ ፍሩት ፋብሪካ" መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ብዙነህ ጉታ በበኩላቸው በቀን 80 ቶን አቮካዶ ዘይት የሚያመርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በፓርክ ውስጥ ተክለዋል።

ፋብሪካው ለሚጠቀመው ግብዓት ከስምንት ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ጋር የገበያ ትስስር መፍጠሩን ጠቁመዋል።
ባለሀብቶቹ እንደሚሉት ፓርኩ መሰረተ ልማት ያሟላ በመሆኑ እሴት የተጨመረባቸውን ምርቶች በቀላሉ ለማምረት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል።
ይህም ለዘርፉ እመርታና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አንስተዋል።

የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሃይሉ የተራ እንዳሉት እስካሁን በግብርና ምርቶች ማቀነባበር የተሰማሩ ስምንት ፋብሪካዎች ወደስራ ገብተዋል።
ከነዚህም መካከል አራቱ በአቮካዶ ዘይት ምርት መሰማራታቸውን ገልፀው፤ የአቮካዶ ጥሬ ምርቶችን ከአርሶ አደሩ በመረከብ የገበያ ትስስር እንደፈጠሩ ገልጸዋል፡፡
ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2 ሺህ 664 ቶን በላይ እሴት የተጨመረበት የአቮካዶ ዘይት ለውጭ ገበያ በማቅረብ 17 ነጥብ 7 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማስገኘታቸውን እንዲሁ።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026