
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2017(ኢዜአ)፦ጥራቱን የጠበቀ የቆዳ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ለሚገኙ ሶስት አምራች ፋብሪካዎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡
እውቅናውን የኢትዮጵያ አምራቾች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት እና የአውሮፓ ሕብረት ናቸው በጋራ የሰጡት፡፡
በእውቅና መርሐ ግብሩ ኢትዮ ሌዘር ኢንዱስትሪ (ኤሊኮ) አዋሽ እና አቢሲኒያ የቆዳ ፋብሪካዎች የወርቅ ተሸላሚ ሲሆኑ ባቱ ደግሞ የብር ደረጃ ተሸላሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አምራቾች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሚሊኬሳ ጃገማ በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ በቆዳ ኢንዱስትሪው ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥራት ያለውና ተወዳደሪ የሆኑ ምርቶችን ለማቅረብ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነች ነው።
ፋብሪካዎቹ በተለይም የምርት ጥራትን፣ የሰራተኛና የአካባቢ ደህንነትን በመጠበቅ እንዲሁም በአጠቃላይ አለም አቀፍ መስፈርቶችን በማሟላታቸው እውቅና ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፥ በቆዳ ሀብት ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት መንግስት ከሚሰራቸው ሰራዎች በተጨማሪ በሴክተሩ ያሉ የባለድርሻ አካላት ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) በቆዳ ዘርፍ ዘላቂ የስራ እድል ለመፍጠር የሚሰራ ኢኒሼቲቭ አስተዳደር አውሬሊያ ካላብሮ በበኩላቸው ዩኒዶ የቆዳው ዘርፍ ላይ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀዋል።
የቆዳ ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የዘርፉን ማህበር ማጠናከርና የቆዳ ምርታማነትን በማሳደግ ዘላቂነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026