የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የቆዳ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ለሚገኙ ሶስት አምራች ፋብሪካዎች እውቅና ተሰጠ</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2017(ኢዜአ)፦ጥራቱን የጠበቀ የቆዳ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ለሚገኙ ሶስት አምራች ፋብሪካዎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡


እውቅናውን የኢትዮጵያ አምራቾች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት እና የአውሮፓ ሕብረት ናቸው በጋራ የሰጡት፡፡


በእውቅና መርሐ ግብሩ ኢትዮ ሌዘር ኢንዱስትሪ (ኤሊኮ) አዋሽ እና አቢሲኒያ የቆዳ ፋብሪካዎች የወርቅ ተሸላሚ ሲሆኑ ባቱ ደግሞ የብር ደረጃ ተሸላሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ አምራቾች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሚሊኬሳ ጃገማ በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ በቆዳ ኢንዱስትሪው ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥራት ያለውና ተወዳደሪ የሆኑ ምርቶችን ለማቅረብ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነች ነው።


ፋብሪካዎቹ በተለይም የምርት ጥራትን፣ የሰራተኛና የአካባቢ ደህንነትን በመጠበቅ እንዲሁም በአጠቃላይ አለም አቀፍ መስፈርቶችን በማሟላታቸው እውቅና ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡


ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፥ በቆዳ ሀብት ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት መንግስት ከሚሰራቸው ሰራዎች በተጨማሪ በሴክተሩ ያሉ የባለድርሻ አካላት ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።


የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) በቆዳ ዘርፍ ዘላቂ የስራ እድል ለመፍጠር የሚሰራ ኢኒሼቲቭ አስተዳደር አውሬሊያ ካላብሮ በበኩላቸው ዩኒዶ የቆዳው ዘርፍ ላይ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀዋል።


የቆዳ ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የዘርፉን ማህበር ማጠናከርና የቆዳ ምርታማነትን በማሳደግ ዘላቂነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026