የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

<p>የቆዳ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ለሚገኙ ሶስት አምራች ፋብሪካዎች እውቅና ተሰጠ</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 27/2017(ኢዜአ)፦ጥራቱን የጠበቀ የቆዳ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ለሚገኙ ሶስት አምራች ፋብሪካዎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡


እውቅናውን የኢትዮጵያ አምራቾች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት እና የአውሮፓ ሕብረት ናቸው በጋራ የሰጡት፡፡


በእውቅና መርሐ ግብሩ ኢትዮ ሌዘር ኢንዱስትሪ (ኤሊኮ) አዋሽ እና አቢሲኒያ የቆዳ ፋብሪካዎች የወርቅ ተሸላሚ ሲሆኑ ባቱ ደግሞ የብር ደረጃ ተሸላሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ አምራቾች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሚሊኬሳ ጃገማ በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ በቆዳ ኢንዱስትሪው ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥራት ያለውና ተወዳደሪ የሆኑ ምርቶችን ለማቅረብ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነች ነው።


ፋብሪካዎቹ በተለይም የምርት ጥራትን፣ የሰራተኛና የአካባቢ ደህንነትን በመጠበቅ እንዲሁም በአጠቃላይ አለም አቀፍ መስፈርቶችን በማሟላታቸው እውቅና ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡


ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፥ በቆዳ ሀብት ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት መንግስት ከሚሰራቸው ሰራዎች በተጨማሪ በሴክተሩ ያሉ የባለድርሻ አካላት ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።


የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) በቆዳ ዘርፍ ዘላቂ የስራ እድል ለመፍጠር የሚሰራ ኢኒሼቲቭ አስተዳደር አውሬሊያ ካላብሮ በበኩላቸው ዩኒዶ የቆዳው ዘርፍ ላይ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀዋል።


የቆዳ ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የዘርፉን ማህበር ማጠናከርና የቆዳ ምርታማነትን በማሳደግ ዘላቂነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025