የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የመከላከያ አጠቃላይ አቅሞች ኢትዮጵያ እያንሰራራችና አስተማማኝ አቅም ላይ እንዳለች ያመለክታሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት30/2017(ኢዜአ)፦ የመከላከያ አጠቃላይ አቅሞች ኢትዮጵያ እያንሰራራች እና አስተማማኝ አቅም ላይ እንዳለች በግልጽ እንደሚያመላክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያን ለመጠበቅ የሚያስችል ከፍተኛ ብቃት እንዳለ የሚያረጋግጥም ነው ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪን ዛሬ መርቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢንዱስትሪውን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ዛሬ እየተመረቱ ያሉ ድሮኖች ከጥቂት ዓመታት በፊት ለማምረት የማይታሰቡ እንደነበሩ አውስተዋል።

በትልም መልክ ተቀምጠው የነበሩ አዳዲስ የጦር አቅሞች እና አቅም አባዢ መሳሪያዎችን በራስ ገንዘብ ገዝቶ ለመታጠቅ አዳጋች እንደነበር ገልጸዋል።

ሰው አልባ ድሮኖች ተግዝተው ወደ ሀገር ቤት ከመጡ በኋላም በሚፈለገው አቅም ለመጠቀም ውስነነቶች እንደነበሩም ተናግረዋል።

በዓለም ደረጃ የውጊያ መልክ ተቀይሮ ወደ አራተኛው ትውልድ ጦርነት እየተገባ መሆኑ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሰው አልባ አውሮፕላኖች እና በሌሎች ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች አቅምን ማጉልበት ቁልፍ መሆኑ ታምኖበት በመንግስት በኩል በከፍተኛ ትኩረት ሲሰራበት መቆየቱን አመልክተዋል።


በአጭር ጊዜ ውስጥ በከፍተኛ ትጋት በተከናወነ ስራ በኢትዮጵያዊያን እውቀት፣ የሰው ኃይል እና የቴክኖሎጂ አቅም የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ማምረት መቻል መጀመሩ ትልቅ እመርታ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የታገዙት ድሮኖች ጦርነትን ማስቀረት ብቻ ሳይሆን ጦርነትን ባጠረ ጊዜ ለመጨረስ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።

ቴክኖሎጂው ለመከላከያ፣ የፖሊስ ኃይል እና ደህንነት ዘርፉ ተደማሪ አቅምን የሚፈጥር መሆኑን አመልክተዋል።

ቴክኖሎጂ በባህሪው ሁልጊዜ አዳጊ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርምርን ማስቀጠል፣ ገበያን ማምጣት እና የተቋማትን የቅንጅት አሰራር ማጎልበት እንደሚገባ አሳስበዋል።

መንግስት በስትራቴጂው ኢትዮጵያ በዓለም የድሮን ገበያ ድርሻ እንዲኖራት ማስቀመጡንና ይህንንም እውን ለማድረግ ገበያን ማፈላለግ አበክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

የመከላከያ አጠቃላይ አቅሞች ኢትዮጵያ እያንሰራራች እና አስተማማኝ አቅም ላይ እንዳለች በግልጽ እንደሚያመላክቱ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያን ለመጠበቅ የሚያስችል ከፍተኛ ብቃት እንዳለ የሚያረጋግጥም ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ያላትን አቅም አሟጦ በመጠቀም ያላትን ከፍታ ለማላቅ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ብልጽግናን እውን ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026