የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ማዕከል በመስራት ይቻላልን በተግባር አሳይተናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ማዕከል በመስራት ይቻላልን በተግባር ያሳየነውን ያህል ተጠቃሚነታችንን ማረጋገጥ ይኖርብናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ማዕከሉ 205 ቢሊዮን የተፈቀደ ካፒታል እንዳለው ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በስኬት መጠናቀቅ የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ያዘጋጀው የእውቅናና ምስጋና መርሀ ግብር ተካሂዷል።

በመርሀ ግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዳሉት፤ የማዕከሉ ግንባታ የተጀመረው ከለውጡ በፊት ቢሆንም በተጨባጭ ተግባራዊ የተደረገው በለውጡ መንግስት ነው።


የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ስራዎችን በተናጠል ማከናወን ከባድ፤ በጋራ ሲከናወኑ ደግሞ ቀላል እንደሆኑ በተግባር ያሳየ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የማዕከሉ ግንባታ ወጭ 96 ነጥብ 2 በመቶ በከተማ አስተዳደሩ የተገነባ መሆኑን አውስተው፤ በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ሌሎች ተቋማትም ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ 21 የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ሌሎች የአካባቢው አርሶ አደሮች ከእኛ ሀገር ይቀድማል ብለው ቦታቸውን ለቀውልናል ብለዋል።

ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ማዕከል መገንባት የተቻለው በቅን ኢትዮጵያውያን የላቀ ትጋትና ትብብር መሆኑንም ገልጸዋል።


በመሆኑም አዲስ አበባን የአፍሪካ የስበት ማዕከል ማድረግ የሚያስችል ማዕከል እንዲገነባ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላት የላቀ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

የመገናኛ ብዙሃን፣ የፀጥታ አካላት፣ ሌሎች በሂደቱ የተሳተፉ የመንግስትና የግል ተቋማት ሚናቸው የጎላ በመሆኑ ምስጋና እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ማዕከል መስራት እንደምንችል አሳይተንበታል ያሉት ከንቲባዋ በማዕከሉ ተጠቃሚነታችንን ማረጋገጥ ይኖርብናል ብለዋል።

ከንቲባ አዳነች እንደገለጹት፤ ማዕከሉ 205 ቢሊዮን የተፈቀደ ካፒታል አለው።

ኢትዮጵያውያን የማዕከሉን አክሲዮን በመግዛት ለስኬታማነቱ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025