አዲስ አበባ፤ መጋቢት 01/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የኢኮኖሚ ስብራትን በመጠገን ለወጣቶች ክህሎት ልማት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢንዱስትሪ እና የክህሎት ልማት ሥራ ለሀገር ዕድገት የማይነጣጠል ሚና እንዳላቸውም በመድረኩ ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዘጋጅነት "ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች" በሚል መሪ ሀሳብ "ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ" ምዕራፍ ሁለት የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በዚሁ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)፥ "በክህሎት የበቃ የሰው ሃይል፥ ለአንድ ሀገር ምን አስተዋጽኦ ይኖረዋል" በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡
በጽሁፋቸው ጥራት ያለው ክህሎት የተላበሰ ዜጋን ማፍራት ለአንድ ሀገር የጋራ ትርክት ግንባታ ወሳኝ ጉዳዮች መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም የሀገርን የለውጥ ጉዞ ለማሳካት ገበያ-መር ክህሎትን የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢኮኖሚያዊ ስብራትን ለመጠገንና ለወጣቶች ክህሎት ልማት ቁልፍ ሚና እንዳለው አንስተዋል።
የወጣቶችን ክህሎት የበለጠ ለማበልጸግና ለሀገር ዕድገት ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ለማድረግ ከአምራች ኢንዳስትሪና ከግሉ ዘርፍ አልሚዎች ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል።
የቴክኒክና ሙያ ተግባር ተኮር የትምህርትና ስልጠና ርዕይን እውን ለማድረግ ሕጋዊ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ተባባሪ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራበት መሆኑንም አስረድተዋል።
የመንግስትና የግል ተቋማት በክህሎት ልማት ትብብራቸውን በማጠናከር የኢትዮጵያን ዕድገት የሚያስቀጥል ብቁ የሰው ሃይል ማፍራት የበለጠ እንዲሰሩም ጠይቀዋል።
ኢንዳስትሪ እና ክህሎት ልማትን የሚዳስስ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ የኢንዱስትሪ እና የክህሎት ልማት ሥራ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት የማይነጣጠል ሚና እንዳላቸው ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ የሚፈልገውን ክህሎት የተላበሰ የሰው ሃይል ለማፍራት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በቆዳ፣ ጨርቃ ጨርቅና ሌሎች ዘርፎች የሚሰሩ የኢንዱስትሪ የሚኒስቴር የስልጠና ማዕከላትም ክህሎት የተላበሰ የሰው ሃይል ለማፍራት አዎንታዊ ሚና እየተጫወቱ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የኢንዳስትሪ አቅም ግንባታ ስትራቴጂ በማዘጋጀት ክህሎት መር የግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ኢንዳስትሪ ልማትን ለማሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት ለኢንዱስትሪ ምርታማነት የተሰጠው ትኩረትም በተኪ ምርት ላይ ውጤት በማስመዝገብ የውጭ ምርት ጥገኝነትን ለማስቀረት የሚያስችል መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025