የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የትራፊክ አደጋ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ሶፍትዌር ስራ አስጀመረ

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የትራፊክ አደጋ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ማዘመን የሚያስችል ሶፍትዌር ስራ አስጀመረ፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ እና የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ስራ ላይ የዋለውን ሶፍትዌር በተመለከተ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ጀማል አባሶ በመግለጫው፤ ባለፉት የለውጥ አመታት የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡

በዚህም በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ይደርስ የነበረው የትራፊክ አደጋ ትርጉም ባለው መልኩ ቅናሽ ማሳየቱን ገልጸው፣ ለዚህም የባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ እንደነበር አመላክተዋል፡፡

ነግር ግን በመረጃ አያያዝ ስርዓት ላይ ክፍተቶች አንደነበሩ አንስተው፤ ይፋ የተደረገው ሶፈትዌር ክፍተቶችን በመሙላት የመረጃ አሰባሰብ ስርዓቱን ወደ ዲጂታል የሚቀይር ነው ብለዋል፡፡

ሶፍትዌሩ የመረጃ ታዓማኒነትን የሚያረጋግጥ፣ ጊዜን የሚቆጥብ እና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሶፍትዌሩ ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሙከራ ላይ መቆየቱን ተናግረው፤ በዚህም አስተማማኝነቱ ተረጋግጧል ነው ያሉት።


የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኢንተለጀንስ ዋና መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር ሐብታሙ ካሳ በበኩላቸው፤ ሶፍትዌሩን ለማበልጸግ ሁለት አመታት እንደፈጀ ተናግረዋል፡፡

በዛሬው እለት ስራ ላይ የዋለው ሶፍትዌር የትራፊክ አደጋ ከደረሰበት ስፍራ መረጃ በቀጥታ ወደ ፌደራል ፖሊስ የመረጃ ቋት እንደሚያስገባ ተናግረዋል።

አዲሱ የመረጃ ማሰባሰቢያ ስርዓት እንደ ጤና ተቋማትና ሌሎች መሰል ባለድርሻ አካላት የመረጃ ቋት ጋር የተሳሰረ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2022 ዓ.ም የአፍሪካ ምርጥ የፖሊስ ተቋም ለመሆን የያዘውን እቅድ እውን ለማድረግ እንደሚያግዝም ተናግረዋል።

ሁለቱ ተቋማት በ2016 ዓ.ም የመንገድ ትራፊክ አደጋ መረጃ አያያዝ ሥርዓትን ማዘመን የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026