አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የትራፊክ አደጋ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ማዘመን የሚያስችል ሶፍትዌር ስራ አስጀመረ፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ እና የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ስራ ላይ የዋለውን ሶፍትዌር በተመለከተ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ጀማል አባሶ በመግለጫው፤ ባለፉት የለውጥ አመታት የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል፡፡
በዚህም በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ይደርስ የነበረው የትራፊክ አደጋ ትርጉም ባለው መልኩ ቅናሽ ማሳየቱን ገልጸው፣ ለዚህም የባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ እንደነበር አመላክተዋል፡፡
ነግር ግን በመረጃ አያያዝ ስርዓት ላይ ክፍተቶች አንደነበሩ አንስተው፤ ይፋ የተደረገው ሶፈትዌር ክፍተቶችን በመሙላት የመረጃ አሰባሰብ ስርዓቱን ወደ ዲጂታል የሚቀይር ነው ብለዋል፡፡
ሶፍትዌሩ የመረጃ ታዓማኒነትን የሚያረጋግጥ፣ ጊዜን የሚቆጥብ እና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሶፍትዌሩ ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሙከራ ላይ መቆየቱን ተናግረው፤ በዚህም አስተማማኝነቱ ተረጋግጧል ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኢንተለጀንስ ዋና መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር ሐብታሙ ካሳ በበኩላቸው፤ ሶፍትዌሩን ለማበልጸግ ሁለት አመታት እንደፈጀ ተናግረዋል፡፡
በዛሬው እለት ስራ ላይ የዋለው ሶፍትዌር የትራፊክ አደጋ ከደረሰበት ስፍራ መረጃ በቀጥታ ወደ ፌደራል ፖሊስ የመረጃ ቋት እንደሚያስገባ ተናግረዋል።
አዲሱ የመረጃ ማሰባሰቢያ ስርዓት እንደ ጤና ተቋማትና ሌሎች መሰል ባለድርሻ አካላት የመረጃ ቋት ጋር የተሳሰረ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የቴክኖሎጂ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2022 ዓ.ም የአፍሪካ ምርጥ የፖሊስ ተቋም ለመሆን የያዘውን እቅድ እውን ለማድረግ እንደሚያግዝም ተናግረዋል።
ሁለቱ ተቋማት በ2016 ዓ.ም የመንገድ ትራፊክ አደጋ መረጃ አያያዝ ሥርዓትን ማዘመን የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025