የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

መንግስት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶች ውጤት ታይቶባቸዋል-የወረዳው ነዋሪዎች

Mar 11, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ ፤ መጋቢት 1/2017 (ኢዜአ) ፡- መንግስት የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶች ውጤት የታየባቸው መሆናቸውን በሰሜን ወሎ ዞን የጉባላፍቶ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ።

በዞኑ በጉባላፍቶ ምርጫ ክልል በህዝብ የተወከሉ የክልል ምክር ቤት ተመራጮች ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በወልዲያ ከተማ ምክክር አድርገዋል።

በምክክሩም መንግስት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶች ውጤት እየተመዘገበባቸው መሆኑን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል።

በውይይቱ ላይም የሃራ ከተማው ነዋሪ አቶ ወርቁ ይመር እንዳሉት በከተማዋ ዘርፈ ብዙ የልማት ውጤቶች በመመዝገባቸው ነዋሪውን ተጠቃሚ እያደረጉ ናቸው።

በተለይም የከተማው የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የመብራት አገልግሎት እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎች አበረታች ውጤት ማሳየታቸውን አንስተዋል።

ሌላው የጉባላፍቶ ወረዳ ነዋሪ አቶ ይመር ንጉስ በበኩላቸው በወልዲያ ከተማ የሚገነቡት የአስፋልትና የቀለበት መንገድ ስራዎች የከተማዋን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው ብለዋል።

እነዚህም መንግስት ልማትን በማፋጠን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳዩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በነዳጅ ላይ የሚስተዋለውን ህገወጥ እንቅስቃሴ፣ የኑሮ ውድነትና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መንግስት እንዲፈታ የጠየቁት ደግሞ የውይይቱ ተሳታፊ አቶ እሸቱ ተክሌ ናቸው።


የወልዲያ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ በበኩላቸው ተሳታፊዎች ያነሷቸው ጥያቄዎች ህዝብና መንግስት እየተመካከሩ በጋራ የሚፈቷቸው ናቸው ብለዋል።

የኑሮ ውድነትን ለመፍታት የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በህብረት ስራ ማህበራት በኩል እየቀረቡ መሆናቸውን ጠቁመው ህገወጥ ነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር አዲስ አሰራር ተተግብሯል ብለዋል።

በአማራ ክልል ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ አባልና የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል ወይዘሮ አስናቀች ኃይሌ እንዳሉት የክልልና የተወካዮች ምክር ቤት አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር መወያየታቸው ችግሮችን ለመፍታት የሚያግዝ ነው።


በመድረኩ የተነሱ መልካም አፈጻጸሞችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና የተስተዋሉ ክፍተቶችን ፈጥኖ በማረም የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚያግዙ አስረድተዋል።

መንግስት ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት እንዲችልም ህብረተሰቡ የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት መሪ ተዋናይ እንዲሆን ጠይቀዋል።

በጉባ ላፍቶ ምርጫ ክልል ስር የጉባላፍቶና የአንጎት ወረዳዎች እንዲሁም የወልዲያና የሃራ ከተሞች እንደሚገኙም ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025