
ቦንጋ፤መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦በክልሉ በበልግ ወቅት 359 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የአዝርዕት ሰብሎች እንደሚለማ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ገለፀ።
የቢሮው ምክትል ሀላፊና የእርሻ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አሸናፊ ክንፉ እንዳሉት፥ የበልግ እርሻን ውጤታማ ለማድረግ የግብርና ግብዓትና ቴክኖሎጂን በአግባቡ በመጠቀም እየተሰራ ነው።
በበልግ እርሻ በቆሎ፣ቦሎቄ፣ሩዝ፣ ማሽላና በሌሎች ሰብሎች ከሚለማው 359 ሺህ ሄክታር መሬት ከ13 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ለማምረት መታቀዱን ተናግረዋል።
እስካሁንም ከ173 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በማረስ 25 ሺህ ሄክታሩ በበቆሎ ሰብል መሸፈኑን ገልፀዋል።
ከበልግ ማሳ 30 በመቶው በኩታ ገጠም ለማልማት መታቀዱን ገልጸው፣ ለልማቱም 156 ሺህ 300 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንዲሁም ምርጥ ዘር መቅረቡን አስታውቀዋል።
በክልሉ ካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ በበልግ አዝመራ በተለያዩ ሰብሎች 8ሺህ 650 ሄክታር ማሳ በማልማት 311 ሺህ 400 ኩንታል ምርት ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የወረዳው ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ መለሰ መንገሻ ናቸው።
እስካሁኑ ከ6 ሺህ ሄታር በላይ ማሳ መታረሱን ጠቁመው፥ አጠቃላይ ከሚለማው ማሳም 7 ሺህ 36 ሄክታሩ በበቆሎ እንደሚሸፈን አመልክተዋል።
በወረዳው የጨበራ ቀበሌ አርሶ አደር አየለች አባጊሶ በበኩላቸው፥ ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በበልግ እርሻ በበቆሎ ሰብል በመሸፈን 60 ኩንታል ለማምረት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
በግብርና ባለሙያዎችና በየደረጃው ባሉ አመራሮች ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ጠቅሰው፥ ይህም የተሻለ ምርት ለማምረት ያስችለኛል ብለዋል።
ሌላው የቀበሌው አርሶ አደር ናስር አባቡልጉ፥ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ተጠቅመው በሁለት ሄክታር ማሳ በቆሎ ለማምረት የእርሻ ስራቸውን እያከናወኑ መሆኑንና 80 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
የዝናብ መዘግየት ሥራው በተወሰነ ጊዜ ዘግይቶ እንዲጀመር ማድረጉን ጠቁመው፣ አሁን መጣል የጀመረውን ዝናብ ተጠቅመው ማሳቸውን በዘር እንደሚሸፍኑ ገልጸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026