አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩባቸውን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ከአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ እና ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮች ጋር በመሆን በስልጠና ላይ የሚገኙ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፖችን) ጎብኝተዋል።
ዶክተር አህመዲን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ቴክኖሎጂ የሥራ ፈጠራና ክህሎት ለውጥ መሪ ቁልፍ በመሆኑ ዘርፉን ማበረታታት፣ የወጣቶችን ዕምቅ ችሎታ ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን አመቺ ሁኔታን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
እየተሰጠ ያለው ስልጠናም የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ የሚያጠናክርና ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በኢንስቲትዩቱ የሚገኘውን ሜከርስፔስ (BiTec) የሚገኙ ከሀሳብ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡ የተለያዩ ችግር ፈች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጎብኘታቸውን አመልክተዋል።
ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩበትን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የገለጹት ዶክተር አህመዲን፤ በስልጠናው ከፍተኛ ሚና ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦችን አመስግነዋል።
ለስታርትኦፕች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል በመልዕክታቸው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025