
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩባቸውን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ከአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ እና ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮች ጋር በመሆን በስልጠና ላይ የሚገኙ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፖችን) ጎብኝተዋል።
ዶክተር አህመዲን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ቴክኖሎጂ የሥራ ፈጠራና ክህሎት ለውጥ መሪ ቁልፍ በመሆኑ ዘርፉን ማበረታታት፣ የወጣቶችን ዕምቅ ችሎታ ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን አመቺ ሁኔታን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
እየተሰጠ ያለው ስልጠናም የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ የሚያጠናክርና ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

በኢንስቲትዩቱ የሚገኘውን ሜከርስፔስ (BiTec) የሚገኙ ከሀሳብ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡ የተለያዩ ችግር ፈች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጎብኘታቸውን አመልክተዋል።
ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩበትን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የገለጹት ዶክተር አህመዲን፤ በስልጠናው ከፍተኛ ሚና ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦችን አመስግነዋል።
ለስታርትኦፕች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል በመልዕክታቸው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026