የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩባቸውን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ ያስፈልጋል- አህመዲን አህመድ (ዶ/ር)

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩባቸውን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

አህመዲን አህመድ (ዶ/ር) ከአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ እና ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮች ጋር በመሆን በስልጠና ላይ የሚገኙ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፖችን) ጎብኝተዋል።

ዶክተር አህመዲን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ቴክኖሎጂ የሥራ ፈጠራና ክህሎት ለውጥ መሪ ቁልፍ በመሆኑ ዘርፉን ማበረታታት፣ የወጣቶችን ዕምቅ ችሎታ ወደ ተግባር የሚቀይሩበትን አመቺ ሁኔታን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብለዋል።

እየተሰጠ ያለው ስልጠናም የወጣቶችን የፈጠራ ሃሳብ የሚያጠናክርና ተጨማሪ አቅም የሚፈጥርላቸው መሆኑን ገልጸዋል።


በኢንስቲትዩቱ የሚገኘውን ሜከርስፔስ (BiTec) የሚገኙ ከሀሳብ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡ የተለያዩ ችግር ፈች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጎብኘታቸውን አመልክተዋል።

ወጣቶች ሀሳባቸውን ወደ ሀገራዊ ፋይዳ የሚቀይሩበትን ማዕከላት እና የፈጠራ ስነምህዳሩን ምቹ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የገለጹት ዶክተር አህመዲን፤ በስልጠናው ከፍተኛ ሚና ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦችን አመስግነዋል።

ለስታርትኦፕች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል በመልዕክታቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026